የ11ኛው ክልል ፈተናዎች - የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ነጋሽ ዋጌሾ ማብራሪያ (ክፍል 1)
Автор: Ethiopia Insider
Загружено: 2022-08-16
Просмотров: 209
Описание:
ከደቡብ ክልል ተነጥሎ ራሱን የቻለ ክልል ከሆነ ዘጠኝ ወራትን ያሳለፈው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፤ በበጀት ውስንነት ምክንያት “ትልቅ ችግር” እንዳጋጠመው የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ ተናገሩ። የክልሉ መንግስት ያጋጠመው የበጀት ጫና፤ የአዳዲስ ሰራተኞችን ቅጥር ጭምር እንዲያቆም አስገድዶታል ተብሏል።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ይህን የገለጹት፤ በክልሉ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ ነሐሴ 3 በሰጡት ማብራሪያ ነው። ያለፉት ሰባት ወራት የክልሉ መንግስት የስራ አፈጻጸም ሪፖርትን ተከትለው የቀረቡት አብዛኞቹ የምክር ቤት አባላት ጥያቄዎች፤ ከመንገድ እና ድልድይ ግንባታዎች እንዲሁም ከመጠጥ ውሃ አቅርቦት ጋር የተያያዙ ነበሩ።
የምክር ቤቱ አባላት በተደጋጋሚ ላነሷቸው የመሰረት ልማት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፤ “በመንገድ፣ በድልድይ እና በውሃ በኩል የሚስተዋለው ትልቁ ችግር የበጀት ውስንነት ነው” ብለዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ስር ባሉ ዞኖች ያለው አጠቃላይ የመንገድ መሰረት ልማት ስርጭት “በጣም ዝቅተኛ” መሆኑን የጠቀሱት ዶ/ር ነጋሽ፤ በፌደራል መንግስትም ሆነ በክልሉ የመንገዶች ባለስልጣን እየተሰሩ ያሉ መንገዶች ግንባታቸው ከተጀመረ ረጅም ዓመታት በማስቆጠሩ በአሁኑ ወቅት በጀታቸው “በጣም ከፍተኛ” መሆኑን ገልጸዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ዝርዝሩን በጹሁፍ ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/7553/
___________________________________________________
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ http://ethiopiainsider.com
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር ፦ / ethiopiainsider
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: