የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ከክልል አደረጃጀት ጋር በተያያዘ ያሳለፈውን ውሳኔ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አስገባ
Автор: Ethiopia Insider
Загружено: 2022-08-15
Просмотров: 554
Описание:
የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ከክልል አደረጃጀት ጋር በተያያዘ ያሳለፈውን ውሳኔ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ማስገባቱን የዞኑ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አርሽያ አህመድ አስታወቁ። የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ውሳኔውን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ማስገባቱን የፌዴሬሽን ምክር ቤት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ተረፈ በዳዳ ለ“ኢትዮጰያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል።
የዞኑ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ውሳኔው ለፌዴሬሽን ምክር ቤት መግባቱን ያስታወቁት፤ ውሳኔውን ካስገቡ በኋላ ከሌሎች የዞኑ ምክር ቤት አመራሮች ጋር በመሆን ዛሬ ሰኞ ነሐሴ 9፤ 2014 በአዲስ አበባ በሰጡት መግለጫ ነው። ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፅህፈት ቤት ገቢ የተደረገው ደብዳቤ፤ የጉራጌ ዞን ከሌሎች መዋቅሮች ጋር በ “ክላስተር” የመደራጀት ምክር ሀሳብን የዞኑ ምክር ቤት በአብላጫ ድምፅ ውድቅ ማድረጉን ይገልፃል።
አፈ ጉባኤ አርሽያ በጉራጌ ዞን በሚገኙ የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር ምክር ቤቶች በጉባኤዎቻቸው ያሳለፏቸውን ውሳኔዎች በተመለከተ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ፤ “በአጀንዳ ይዘን የሁሉም አካባቢ ተወካይ በተገኘበት ነው ጉባኤ ያካሄድነው፡፡ እኔ ከዛ ውጭ እየተካሄዱ ያሉ ጉባኤዎች ላይ አስተያየት ለመስጠት እቸገራለሁ የሚመለከተው አካል አለ ራሱ ከህግ አንጻር ሂዶበት እየሆኑ ያሉ ጉባኤዎች ላይ መልስ መስጠት ይችላል” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
የጉራጌ ዞን ምክር ቤት አመራሮች የምክር ቤቱን ውሳኔ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ካስገቡ በኋላ የሰጡትን ማብራሪያ ከታች ከቪዲዮው ይመልከቱ። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
--------------------------------------------------------------------------------------------------
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ http://ethiopiainsider.com
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር ፦ / ethiopiainsider
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: