በኢትዮጵያ ቤት ወይም መኪና ለመግዛት የፈለገ አንድ ሰው ከባንክ ብድር ለማግኘት ማሟላት ያለበት መስፈርት ምንድን ነው?
Автор: Sheger FM 102.1 Radio
Загружено: 2026-01-02
Просмотров: 4475
Описание:
ታህሳስ 25/2018
በኢትዮጵያ ቤት ወይም መኪና ለመግዛት የፈለገ አንድ ሰው ከባንክ ብድር ለማግኘት ማሟላት ያለበት መስፈርት ምንድን ነው?
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በቅርቡ የቤትና የመኪና ብድር ፈላጊዎችን የሚያስተናግድበትን መመሪያ ማውጣቱን ይፋ አድርጓል፡፡
በመመሪያው መሰረት ፡-
• ቤት ለመስራት ወይም ለመግዛት ቅድሚያ በብድር ከሚጠየቀው ገንዘብ 50 በመቶውን መቆጠብ ያስፈልጋል፡፡
• ለሚገዛው ወይም ለሚገነባው ቤት ከሚጠየቀው ብድር 200 በመቶ ዋጋ የሚያወጣ ቤት ባንኩ ማስያዣ ይፈልጋል፡፡
• በባንክ የሚያዘው ቤት መንገድና የተለያዩ መሰረተ ልማቶች የተነገቡበት አካባቢ ላይ ያለ መሆን አለበት፡፡
• ተበዳሪው በ10 አመት ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ብድሩን ለባንኩ መመለስ አለበት፡፡
• ከሶስት እስከ 6 ወር በሚሰጠው የእፎይታ ጊዜም ጭምር ወለዱን (14 በመቶ) መክፈል ከተበዳሪው ይጠበቃል፡፡
• የተቀመጠው የ14 በመቶ የብድር ወለድ እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ ሊደረግበት ይችላል፡፡ ተበዳሪውም በተስተካከለው ወለድ መሰረት መክፈል ይኖርበታል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..
ትዕግስት ዘሪሁን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : / @shegerfm1021radio
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ / sheger102.1
WhatsApp : https://whatsapp.com/channel/0029VaAO...
X : https://x.com/shegerfm?s=2
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: