በደቡብ ወሎ ዞን ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባው የኩሩ የመስኖ ፕሮጀክት የፌደራል እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተመረቀ
Автор: Amhara Agriculture Bureau
Загружено: 2025-07-30
Просмотров: 1469
Описание:
ድምፅና ምስል ቅንብር ኤዲተር : ጌታቸው ታፈረ
በደቡብ ወሎ ዞን ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባው የኩሩ የመስኖ ፕሮጀክት የፌደራል እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተመረቀ
ደሴ: ሐምሌ13 /2017 ዓ. ም (ግብርና ቢሮ) በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ዙርያ ወረዳ ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባዉ የኩሩ መስኖ ፕሮጀክትን በግብርና ሚኒስቴር የባለአነስተኛ ይዞታ መሬት ልማት ፕሮጀክት መሪ ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ኤሊያስ አወል እና የግብርና ቢሮ ዳይሬክቶሬቶች በተገኙበት በደሴ ዙርያ ወረዳ በ040 ቀበሌ ተመርቋል።
ፕሮጀክቱን የግብርና ቢሮ የባለአነስተኛ ይዞታ መሬት ልማት ፕሮጀክት ሰርቶ በማጠናቀቅና በማስመረቅ በቀበሌው ለሚኖሩ የመስኖ ተጠቃሚ ማህበረሰብ ርክክብ አድርጓል።
በመርሃ ግብሩ የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አሊ መኮንን፣ የአማራ ክልል ማዕድን ቢሮ ሀላፊ አቶ ሃይሌ አበበ፣ በግብርና ሚኒስቴር የባለአነስተኛ ይዞታ መሬት ልማት ፕሮጀክት መሪ ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ኤሊያስ አወል እና የዴስክ ቡድን መሪ ዘለቀ በላይ፣ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ዳይሬክቶሬቶች፣ የደቡብ ወሎ ዞንና የደሴ ዙሪያ ወረዳ አመራሮች፣ የሚመለከታቸው የስራ ክፍል ሀላፊዎች፣ ባለሙያዎች እና በ040 ቀበሌ የሚኖሩ ማህበረሰብ ተገኝተዋል።
የኩሩ መስኖ ፕሮጀክት በግብርና ቢሮ የባለአነስተኛ ይዞታ መሬት ልማት ፕሮጀክት (SHIDP) ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባ መሆኑን በግብርና ቢሮ የባለአነስተኛ ይዞታ መሬት ልማት ፕሮጀክት (SHIDP) አስተባባሪ ኢንጂነር ሙጨ ደመቀ ገልጸዋል። ከ85 ሄክታር መሬት ማሳ በላይ ማልማት እደሚችል እና በመስኖ ፕሮጀክቱ ከ146 በላይ አባወራ እና እማወራዎችን በልማቱ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ የፕሮጀክት አስተባባሪው ኢንጂነር ሙጨ ደመቀ ተናግረዋል።
ዘጋቢ:- አሻግረው ፈረደ
ድምፅና ምስል ቅንብር ኤዲተር : ጌታቸው ታፈረ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ
ድረ-ገጽ http://www.amhboard.gov.et/
ቴሌግራም https://t.me/AmharaBureauofAgriculter
ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?...
ዩትዩብ / @amharaagriculturebureau6055
ቲክቶክ / amhara.agricultur
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: