የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ደዋጨፋ ወረዳ የሙዝ፣ የፓፓያ እና ሌሎች የፍራፍሬ ክላስተሮችን ጎብኝተዋል።
Автор: Amhara Agriculture Bureau
Загружено: 2026-01-01
Просмотров: 121
Описание:
ደዋጨፋ፣ ታህሳስ 19፣ 2018 ዓ/ም ( ግብርና ቢሮ ) የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ደዋጨፋ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች እየለማ ያለን የሙዝ፣ የፓፓያ እና ሌሎች የፍራፍሬ ክላስተሮችን ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ መርሃ ግብር የአመራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋንቱ ተስፋየ፣ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የገጠር ልማት ዘርፍ አስተባባሪ ዶ/ር ድረስ ሳህሉ፣ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ፍስሀ ደሳለኝ፣ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ደረጀ ማንደፍሮ፣ አቶ ከፍያለው ሙላቴ በክልሉ ምክር ቤት የግብርና ፣ የውሃና አካባቢ ጥበቃ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ፣ አቶ ቀለመወርቅ ምህረቴ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተደድር የኢኮኖሚ አማካሪ እንዲሁም የዞን አስተዳዳሪዎች፣ የፓርቲ ሀላፊዎች፣ ምክትል ቢሮ ሀላፊዎች፣ ዳይሬክተሮች፣ የዞን የግብርና መምሪያ ሀላፊዎች እና የዞን ቡድን መሪዎች ጎብኝተዋል።
የጉብኝቱ ተሳታፊዎች እንዳሉት በዛሬው እለት የተመለከትነው የኦሮሞ ብሔረስብ አስተዳደር ዞን ደዋጨፋ ወረዳን ጨምሮ አማራ ክልል በፍራፍሬ ልማት ትልቅ አቅምና ፀጋ እንዳለው የተረዱበት፣ ለዘርፉ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶ ከተሰራ ክልሉ ከራሱ ፍጆታ አልፎ ለሌሎች መትረፍ እንደሚችል በተግባር ያዩበት ጎብኝት ስለመሆኑ ገልፀዋል።
ዘጋቢ:- አንተነህ ሰውአገኝ
ካሜራ:- ጌታቸው ታፈረ
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: