7ኛ ትምህርት :- መጽሐፍ ኢያሱ - የመጨረሻ ታማኝነት፣ በጦርነት ቀጠና ውስጥ አምልኮ
Автор: Washington DC Ethi. Seventh_day Adventist Church
Загружено: 2025-11-12
Просмотров: 57
Описание:
ለዚህ ሳምንት ጥናት የሚከተሉትን ጥቅሶች ያንብቡ፡- ኢያሱ 5:1-7፣ ዘጸ. 12:6፣ 1 ቆሮ. 5:7፣ ኢያሱ 8:30-35፣ ዘዳ. 8:11፣ 14፣ ዕብ. 9:11-12።
የመታሰቢያ ጥቅስ፡ “ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።” (ማቴዎስ 6፡33)
በዚህ ሳምንት እስራኤላውያን በተስፋይቱ ምድር በገቡበት ወቅት፣ እራሳቸውን እንደገና ለጌታ ያስረከቡበትንና በአደጋ ውስጥ ሆነው እንኳን ይህንን ያደረጉባቸውን አንዳንድ ቁልፍ ጊዜያት እንመለከታለን።
ኢያሱ እስራኤላውያን በጠላት ቀጠና ውስጥ እንዲገረዙ በማድረግ(ኢያሱ 5፡ 1-9)፣ ሊመጣ በሚችለው አደጋ ውስጥ እንኳን ፋሲካ እንዲከበር በማድረግ (ኢያሱ 5፡10-12)፣ ድል በመንሣት ላይ ሳሉ መሠዊያ በመሥራት እግዚአብሔርን እንዲያመልኩ በማድረግ (ኢያሱ 8፡30-35)፣ በእስራኤልም የነበሩት ሰባት ነገዶች ርስታቸውን ገና ሳይቀበሉ የእግዚአብሔርን ድንኳን በመትከል (ኢያሱ 18፡1-2) ምክንያታዊ ያልሆኑ የሚመስሉ ውሳኔዎችን ወሰነ።
በተጨናነቀ ህይወታችን ውስጥ፣ ህይወት በእኛ ላይ ለምታመጣቸው አጣዳፊ ነገሮች ትኩረት እንሰጣለን። ብዙ ጊዜ ለእግዚአብሔር ያለንን ቁርጠኝነት ለማደስ እና እሱ ላደረገልን እና በየቀኑ ስለሚያደርግልን ነገሮች ቆም ብለን ምስጋናችንን ለመግለጽ ጥራት ያለው ጊዜ ለመስጠት ስንቸገር እንታያለን። የጠዋት እና የማታ አምልኮ፣ እንዲሁም የቤተሰብ መሠዊያ፣ በእኛ ከልክ በላይ በተጨናነቀ፣ በምቾት ላይ በተመሰረተ፣እና ስኬትን መሰረት ባደረገው ህይወታችን ውስጥ ከአውድ ውጪ የሆኑ ይመስላሉ። ሆኖም ሁላችንም በልባችን ውስጥ፣ ከእግዚአብሔር እና ከምንወዳቸው ሰዎች ጋር አብረን የምናሳልፋቸው ጊዜያት በውስን ጊዜያችን ውስጥ የምናሳልፋቸው ምርጥ ጊዜያት እንደሆኑ እናውቃለን።
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: