ስለ 12ኛ ክፍል ፈተና ዝቅተኛ ውጤት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፓርላማ ምን አሉ?
Автор: Ethiopia Insider
Загружено: 2023-11-14
Просмотров: 36917
Описание:
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በዛሬው ዕለት በፓርላማ በነበራቸው ቆይታ ከቀረቡላቸው ጥያቄዎች መካከል፤ በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የተመዘገበውን ዝቅተኛ ውጤት የተመለከተው ይገኝበታል። ጥያቄውን ያቀረቡት ሱመያ ደሳለው የተባሉ የፓርላማ አባል፤ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የመማሪያ መጽሐፍት “ህትመት እና አቅርቦት ባልተሟላበት” ሁኔታ “የፈተና ስርዓትን ብቻ በመለወጥ የሚፈለገውን የትምህርት ጥራት ማምጣት አይቻልም” ብለዋል። የ2015 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት፤ “ይህን በግልጽ ያመላከተ እና ተማሪዎች እና ወላጆች ላይ ከፍተኛ ጫና እንዲፈጠር ያደረገ ነው” ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል።
የፓርላማ አባሏ፤ ከዚህ ችግር ለመውጣት እና የተማሪዎችን ውጤታማነት ለማሳደግ በመንግስት በኩል የታሰበውን ጠይቀዋል። የ12ኛ ክፍል ፈተናን ያለፉ ተማሪዎች ዕጣ ፈንታን በተመለከተም ተጨማሪ ጥያቄ ሰንዝረዋል። ለጥያቄው ምላሽ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ፤ የፈተናው ውጤት “ከሞላ ጎደል የሚጠበቅ ነው” ብለዋል። “የምንፈትንበት መንገድ ተቀየረ እንጂ ፈተናው ያው ነው፤ ጊዜውም ያው ነው። [የአሁኑ] ትንሽ ቁጥጥር በዛበት” ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ ትምህርት ዘርፉ እና የፈተና ውጤትን በተመለከተ የሰጧቸውን ማብራሪያዎች ከቪዲዮው ይመልከቱ።
----------------------------------------------------------------------------------------------------
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ http://ethiopiainsider.com
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaInsiderNews
ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: