DW Amharic የጥር 29 ቀን 2018 የዓለም ዜና
Автор: DW Amharic
Загружено: 2026-02-06
Просмотров: 3670
Описание:
የጥር 29 ቀን 2018 የዓለም ዜና
• ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥት እና በህወሓት መካከል የበረታውን ውጥረት ለመፍታት “የሰከኑ ውይይቶች” እንደሚያስፈልጉ አሳሰበች።
• የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አባል የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ በመጪው ግንቦት በሚካሔደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እንደማይሳተፉ አስታወቁ።
• በደቡብ ሱዳን ጆንጌሌ ግዛት የታጠቁ ወሮበሎች ትላንት ሐሙስ ሕጻናት አድን የተባለ የብሪታኒያ የግብረ-ሰናይ ድርጅት ጤና ጣቢያ ማውደማቸውን፣ ቢሮውን ማጋየታቸውን እና መዝረፋቸውን ተቋሙ አስታወቀ።
• በምሥራቅ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በሚገኘው የኪሳንጋኒ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት “የሽብር ድርጊት” ሊባል እንደሚችል የአፍሪካ ኅብረት አስታወቀ።
• በፓኪስታን ዋና ከተማ ኢዝላማባድ በአንድ መስጂድ ውስጥ አጥፍቶ ጠፊ በፈጸመው ጥቃት 31 ሰዎች ሲገደሉ ከ170 በላይ ቆሰሉ።
• የሩሲያ ጦር ሠራዊት የወታደራዊ ሥለላ ምክትል ኃላፊ ዛሬ በሞስኮ በጥይት ተመተው ቆሰሉ። ሉቴናንት ጄኔራል ቭላዲሚር አሌክሴዬቭ በሰሜናዊ ሞስኮ በሚገኝ የመኖሪያ ሕንጻ በተደጋጋሚ በጥይት ከተመቱ በኋላ ሆስፒታል ገብተዋል።
• ዩናይትድ ስቴትስ ከ14 ዓመታት በፊት በሊቢያ በሚገኝ ኤምባሲዋ ላይ በተፈጸመ ጥቃት እጁ አለበት ያለችውን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ሥር እንዳዋለች የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታወቁ።
• የጀርመን መራኄ መንግሥት ፍሬድሪሽ ሜርስ የኢራን መሪዎች ከአሜሪካን ጋር ብርቱ ድርድር ማድረግ እንደሚኖርባቸው ጥሪ አቀረቡ።
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: