ንስሐ New Ethiopian Ortodox sibket
Автор: ዜማ ቲዩብ zema tube
Загружено: 2020-10-22
Просмотров: 158
Описание:
Please watch: "ተስፋ አትቁረጡ.መምህር እዮብ ህዝቡን አስለቀሱ #mastewal #እዮብይመኑ #eyobyimenushort #ስብከት #orthodox @zematube127"
• ተስፋ አትቁረጡ | መምህር እዮብ ህዝቡን አስለቀሱ memher eyo... -~-
#ortodox # Ethiopian #ንስሐ
@zematube127 @BalageruTV
👉ንስሐ ፦ ነስሐ ተፀፀተ ካለው የግዕዝ ግስ የወጣ የተገኘ ሲሆን ፤ ንስሐ ማለት በሠሩት ኃጢአት መፀፀት ፣ ማዘን ፣ ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ መወሰን ማለት ነው።
👉ንስሐ ከዘለዓለማዊ ፍርድ የሚያድን ፤ ዘማዊውን እንደ ድንግል ፤ ሌባውን መጽዋች የሚያደርግ በፊት ከተሠራው ኃጢአት ንጹህ አድርጎ ፤ ከእግዚአብሔር ጋር አንድ የሚያደርግ ምሥጢር ነው ።
#የንስሐጥሪ
#ክፍል1
#ክፍል2
ነስሑ እስመ ቀርበት መንግሥተ ሰማያት» (መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ ማቴ ፫፤፩-፪)
«ነስሐ» ስርወ ቃሉ እብራይስጥ ሲሆን ትርጉሙም አዘነ፤ ተጸጸተ፤ ተመለሰ፤ ክፉ ዐመሉን ተወ፤ መጥፎ ጠባዩን ለወጠ ማለት ነው። የግእዙም ግስ ይህንኑ ቃል እንዳለ ወርሶ ይጠቀምበታል።
«ነስሑ እምፍኖቶሙ እኩይ፤ ወእግዚአብሔርኒ ነስሐ እምዘነበበ» ይላል በዮናስ ፫፤፲ ላይ። ከክፉ መንገዳቸው ተመለሱ፤ እግዚአብሔርም በተናገረው ተጸጸተ» እንደማለት ነው። ሰብአ ነነዌ ከኃጢአታቸው በንስሐ በተመለሱ ጊዜ እግዚአብሔርም ሊቀጣቸው በነበረው ፍርድ አዘነና ምህረትን ሰጣቸው። የእግዚአብሔር ሀዘን ከምህረቱ ሲሆን የሕዝቡ ሀዘን ደግሞ ከበደሉ ነው። «ነስሐ» የሚለው ቃል በሁሉም ሥፍራ ማዘንን፤ መመለስን፤ መፀፀትን፤ መተውን ያመለክታል። «እግዚአብሔር ተፀፀተ» ስንል አምላካዊ ምሕረቱን ለመቀበል በማይፈልግ የሰው እልክኛ ልብ ወይም በሌላ መልኩ ምሕረቱን በሚጠይቅ ተነሳሒ ላይ ባለው አባታዊ ፍቅር እንጂ የሚጎድለው ወይም የሚጨመርለት ስላለ ያንን ከማጣትና ከማግኘት ጋር በተያያዘ አይደለም። ሰብአ ነነዌ ከተዘጋጀው ጥፋት ለመመለስ ንስሐ ሲገቡ እግዚአብሔርም በአምላካዊ ምህረቱ አዝኖላቸው ጥፋቱን መልሶላቸዋል። በሌላ ቦታም እንዲህ የሚል አለ።
በዘመነ ኖኅ የሰው ልጅ ዐመጻ በዝቶ የጥፋት ውሃ በታዘዘ ጊዜ «እግዚአብሔርም ሰውን በምድር ላይ በመፍጠሩ ተጸጸተ፥ በልቡም አዘነ» ዘፍ ፮፤፮ ይላል።
«ተጸጸተ» የሚለው ቃል «ነስሐ» የሚለው ቃል ትርጉም ነው። «እግዚአብሔር ተጸጸተ፤ አዘነ» ሲል ቀድሞ ያላወቀው ነገር በመድረሱ ወይም የማያውቀው ነገር እንደተከሰተ በማየቱ የተሰማው ስሜት ሳይሆን የሰው ልጅ ቀድሞ ከገነት ሕጉን አፍርሶ በመውደቁና ዳግመኛም በዚህ ምድር ላይ ኃጢአቱን እያበዛ በመሄዱ የተነሳ ሰው በራሱ በደል የሚመጣበት የፍርድ ቁጣ ስለሚያሳዝነው ብቻ ነው። ፻፳ የንስሐ ዘመንን ለመጠቀም ያልፈለገ ሕዝብ በውሃ ሰጥሞ ሲጠፋ ቢመለከት እግዚአብሔር መጸጸቱ አምላካዊ ባሕሪው ነው። እግዚአብሔር አባት በመሆኑ ሰዎች ይጠፉ ዘንድ ሳይፈልግ ዐመጻቸው ከሚያመጣባቸው ፍርድ የተነሳ ግን ያዝናል፤ ይጸጸታል።
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: