ዳናዊት የተከሰሰችበት የማጭበርበር ወንጀል|አትሌት መሰረት ደፋር ከባድ ሀዘን ገጠማትአዶናይ ያልተጠበቀ ታሪክ ሰራ(
Автор: Gize Media
Загружено: 2026-02-21
Просмотров: 5518
Описание:
የፕሮግራም አስተዋዋቂ ዳናዊት መክብብ እና አራት የሥራ ባልደረቦቿ፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠር የዜጎች ገንዘብ በማጭበርበር ወንጀል ተጠያቂ እንዲሆኑ የቀረበባቸው ክስ በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት መታየት ጀምሯል።
ከአዲስ አበባ የሚሰራጨው ኢትዮፒካ ሊንክ የራዲዮ ፕሮግራም እንደዘገበው፣ ይህ ክስ በዳናዊት ዝና እና በማስታወቂያዎች እውነተኛነት ላይ ከባድ ጥያቄዎችን ያስነሳ ሲሆን፣ የፍትሐ ብሔር ክሱ በዋናነት ያተኮረው "ወደ ውጭ ሀገር እናወጣችኋለን" በሚል ተስፋ ከዜጎች በተሰበሰበ ገንዘብ ላይ ነው።
እንደ ከሳሾች ዝርዝር መረጃ፣ ኤቢኤል ኮንሰልታንሲ (ABL Consultancy) የተባለው ድርጅት፣ ቤተልሔም ታደሰ፣ ገሊላ በለጠ፣ አቤል ተስፋዬ እና ዳናዊት (ወላንሳ) መክብብ ከእያንዳንዱ ተበዳይ 437,000 ብር ተቀብለዋል። ይሁን እንጂ ተከሳሾች ቃላቸውን ባለመጠበቃቸው እና ገንዘቡንም ለመመለስ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው፣ በአጠቃላይ 13 ሰዎች በጋራ በመሆን የሕግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ለፍርድ ቤት አቤቱታቸውን አቅርበዋል።
ይህ ክስ ከዳናዊት ጋር በተያያዘ ትልቅ ትኩረት እንዲያገኝ ያደረገው፣ ተበዳዮቹ ለድርጅቱ ገንዘባቸውን የሰጡት እሷ በሠራችው ማስታወቂያ ላይ ያላቸውን እምነት መሠረት በማድረግ መሆኑ ነው። ክሱ በማስታወቂያ አዋጅ ላይ የተደነገገውን "ማስታወቂያ አስነጋሪ ወይም ወኪሉ የመረጃውን ትክክለኛነት የማረጋገጥ ግዴታ አለበት" የሚለውን ሕግ ዋቢ በማድረግ፣ ዳናዊትም ሆነ ድርጅቱ ለደረሰው ጉዳት በአንድነትና በነጠላ ተጠያቂ መሆን እንዳለባቸው ያሳስባል።
ጉዳዩን እየተመለከተ ያለው የቦሌ ምድብ አራተኛ ፍትሐ ብሔር ችሎት፣ የቀረበለትን የክስ ሰነድ መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለየካቲት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። ይህ የፍርድ ቤት ውሳኔ፣ ታዋቂ ግለሰቦች ለሚያስተዋውቋቸው ድርጅቶች ያላቸውን የሕግ ተጠያቂነት ወሰን የሚያሳይ በመሆኑ በብዙዎች ዘንድ በጉጉት እየተጠበቀ ይገኛል
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: