ጤና ሚኒስቴር የማርበርግ ቫይረስ በሽታን አስመልክቶ የሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ
Автор: Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
Загружено: 2025-11-17
Просмотров: 84746
Описание:
#marburg #virus #news
በማርበርግ ቫይረስ መያዙ የተረጋገጠ በሕይወት ያለ ሰዉ የለም
በአሁኑ ሰዓት በማርበርግ ቫይረስ መያዙ የተረጋገጠ በሕይወት ያለ ሰዉ አለመኖሩን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
እስካሁን ድረስ የሶስት ሰዎች ህይወት በማርበርግ ቫይረስ ምክንያት ህይወታቸዉን ማጣታቸውንም ሚኒስቴሩ ጠቅሷል።
ጤና ሚኒስቴር የማርበርግ በሽታ አስመልክቶ በዛሬው ዕለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እንደገለጹት፤ ሚኒስቴሩ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጂንካ ከተማ የማርበርግ በሽታ መከሰቱን ካሳወቀበት ህዳር 3 ጀምሮ የበሽታዉ ምልክት ያሳዩ ሰዎች ጋር ንክኪ አላቸዉ የተባሉ ሰዎችን ቦታዎች ላይ የመለየት ስራ እየሰራ ይገኛል።
ሚኒስቴሩ እስካሁን ድረስ 17 የላብራቶሪ ናሙና ወስዶ የመረመረ ሲሆን፤ በሶስት ሰዎች ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ ስድስት ሰዎች የበሽታዉን ምልክት አሳይተዉ ህይወታቸዉ ቢያልፍም በላብራቶሪ የተረጋገጠዉ ግን ሶስት ሰዎች ላይ መሆኑን እና እነሱም ህይወታቸዉ ማጣታቸዉን ገልጸዋል።
በአሁኑ ሰዓትም በቫይረሱ መያዙ የተረጋገጠ በሕይወት ያለ ሰዉ እንደሌለ አረጋግጠዋል።
በሽታዉን ለመከላከልም የድንገተኛ የህብረተሰብ ጤና ተቋማት መቋቋማቸዉን እና የላብራቶሪ ግብአቶችና ባለሙያዎች ወደ ቦታዉ መላካቸውን ገልጸዋል።
በአሁኑ ሰዓትም ቁሳቁሶችና መድኃኒቶችን የማሟላት ዝግጅት መጠናቀቁና ግብአት የማሟላትና የማሰራጨት ስራዉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
በበሽታዉ ህይወታቸዉን የሚያጡ ሰዎች ቢኖሩ እንኳን የቀብር ስነ ስርዓት የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በሚሰጠዉ መመሪያ መሰረት መፈጸም እንደሚኖርበትም ጠቁመዋል።
Ethiopian Press Agency /የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: