" መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደሉ" በሐዋሪያ ፍፁም ወ /አረጋይ ,2013 በአዲስ አበባ ቤተክርስቲያን
Автор: Rhema Media One
Загружено: 2021-01-14
Просмотров: 175
Описание:
ቆላስይስ 2 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² ደግሞም ልባቸው እንዲጽናናና በፍቅር እንዲተሳሰሩ፣ ፍጹም የሆነውን የመረዳት ብልጥግና አግኝተው የእግዚአብሔር ምስጢር የሆነውን ክርስቶስን እንዲያውቁ እተጋለሁ፤
³ የተሰወረ የጥበብና የዕውቀት ሀብት ሁሉ የሚገኘው በእርሱ ዘንድ ነውና።
⁴ ማንም ንግግር በማሳመር እንዳያታልላችሁ ይህን እነግራችኋለሁ።
📌 አማኞች የራሱን የክርስቶስን ህይወት ነው የተቀበሉት ይህ ህይወት ደግሞ የማይሸነፍ፣ የማይደክም፣ ክብር የሞላበት ኋያል ህይወት ነው።
📌 እግዚአብሔር የተቀበለን ልጅ አድርጎ ነው ይህ ማለት የእርሱን ህይወት ሰጥቶናል ማለት ነው። እግዚአብሔር ክርስቶስን እንደተቀበለው ያህል ተቀብሎናል።
📌 በመወለድ ያገኘነው ህይወት ፦
👉 ሊጠፋ የማይችል
👉 በምንም የማይወሰድ
👉 የማይበከል
👉 የማይኮነን እፁብ ድንቅ የሆነ ህይወት ነው።
📌 የእግዚአብሔር ፍቃድ ይህንን ህይወት እንድንኖረው እንድንገልፀው ነው።
ተጋድሎ የሚያስፈልገው ይህ ህይወት በሙላት እንዳይገለፅ አእምሮአችን ላይ ዘወትር የማይገበን ሃሳብ ከሚያስገባው የክፉ አሰራር ጋር ነው።
📌 የጦርነቱ ሜዳ የሰው አእምሮ ነው ። አማኞች የክርስቶስን ትምህርት ዘወትር በማስገባት ከክርስቶስ ትምህርት ውጪ ያለውን የዓለም ፣ የሴይጣን፣ የሰውን የማይገባ ሃሳብ ማስወገድ ይጠበቅባቸዋል። ሴይጣን እንደ ምሽግ የሚጠቀመው የሰውን ያልተለወጠ አእምሮ ነው።
📌 ሰለዚህም ፦ “አባቶች ሆይ፤ ከመጀመሪያ ያለውን እርሱን ዐውቃችሁታልና፣ እጽፍላችኋለሁ። ጐበዛዝት ሆይ፤ ብርቱዎች ስለ ሆናችሁ፣ የእግዚአብሔር ቃል በእናንተ ስለሚኖር፣ ክፉውንም ስላሸነፋችሁ፣ ጽፍላችኋለሁ።”
— 1ኛ ዮሐንስ 2፥14 (አዲሱ መ.ት)
ተብሎ እንደተፃፈ በአሸናፊነት ያንን የከበረ ህይወት በመኖር ጌታን እንድናከብርና እንድንገልፀው ዘወትር አእምሮአችንን በእወቀት መሙላት እና ያንን ብቻ በመኖር የእምነትን ገድል መፈፀም ያስፈልገናል።
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: