21 - በደቂቀ እስጢፋ ዙርያ፡ በተደጋጋሚ ለሚነሡ ጥያቄዎች፡ መልስ (በዶ/ር መስከረም ለቺሣ)
Автор: Utopia Media (Official) - Dr. Meskerem Lechissa
Загружено: 2024-02-16
Просмотров: 25911
Описание:
በዚህ ቪድዮ ምላሽ የተሰጠባቸው ጥያቄዎችና የተሳሳቱ አስተሳሰቦች፦
1. “ደቂቀ እስጢፋኖስ የግፍ ጭፍጨፋ ተደርጎባቸዋል” የሚለው አስተሳሰብ፤
2. “ደቂቀ እስጢፋኖስ የተሰደዱትና የተገደሉት፡ እውነተኛውን ወንጌል በማስተማራቸው ምክንያት ነው” የሚባለው አስተሳሰብ፤
3. “ሰው፡ ለማርያም አልሰግድም ስላለ መገደል የለበትም” የሚለው ተቃውሞ፤
4. “ደቂቀ እስጢፋኖስ የተጠሉት የትግራይ ሰዎች ስለኾኑ ነው። የሸዋ ነገሥታት፡ ለትግራይ ተወላጆች ጥላቻና ንቀት የሰሎሞናዊነትም ፉክክር ስለነበረባቸው፡ ጨፈጨፏቸው” ስለሚባለው፤
5. “የኢትዮጵያ የክርስትና ታሪክ በሙሉ የትግራይ ታሪክ ነው። ኢትዮጵያ የምትባል አገር የለችም። ትግራይ ናት። አቡነ ተክለሃይማኖት ትግሬ ናቸው፤ ጃንደረባው ትግሬ ነው፤ አክሱም የትግሬ ናት፤ ደቂቀ እስጢፋኖስም ትግሬዎች ናቸው፤ ንግሥተ ሳባ ትግሬ ናት። ምርጥ ምርጡ ኹሉ ትግሬ ነው። መጥፎ መጥፎዎቹ ግን ኢትዮጵያውያን ናቸው” የሚለው የጽንፈኛ ብሔርተኞች ጥቅል አስተሳሰብ፤
6. ዐጼ ዘርዓ ያዕቆብም፡ ከሰሎሞናዊው ዘር የመጣ ከኾነ፥ ደቂቀ እስጢፋም፡ አይሁድ ከነበሩ፡ እንዴት አይሁድነት ሊያጋጫቸው ቻለ? ኹለቱም ሥረ መሠረታቸው አንድ አይደለም ወይ?
7. “ደቂቀ እስጢፋኖስ ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያውያን ነበሩ” ለሚሉ፤
8. “ደቂቀ እስጢፋኖስ ሰማዕታት ናቸው” ለሚሉ፤
9. “ደቂቀ እስጢፋኖስ፡ አሁን ላሉት ፕሮቴስታንቶች እና ተሃድሶዎች፡ የመንፈስ አባቶች ናቸው፤ ወይም ከማርቲን ሉተር በፊት፡ የተሃድሶ ፕሮቴስታንት እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ በደቂቀ እስጢፋ ነው የተጀመረው” ስለሚለው አስተሳሰብ፤
10. “አባ እስጢፋኖስ ጉንዳጉንዴን ብቻ ሳይኾን፡ ጣና ገዳማትን በሙሉ የገደሙ ትልቅ አባት ናቸው። ኃይቅ እስጢፋኖስን ገድመዋል። መጽሓፈ ሄኖክን ለትውልድ አኑረዋል” ለሚሉ ቀልደኞች፤
11. “ደቂቀ እስጢፋኖስ ለቅድስት ድንግል ማርያም የተለየ ፍቅር ነበራቸው፤ በስሟ የጸሎት መጻሕፍትን ይጽፉላታል፤ በስሟ ገዳማት ገድመውላታል” ለሚሉ ሐሰተኞች፤
12. “ደቂቀ ኤልያስ፣ ደቂቀ እግዚአብሔር፣ ደቂቀ እስጢፋኖስ የሚባሉ እውነተኞች ነበሩ የሚል፡ በመሪ ራስ አማን በላይ መጻሕፍት ውስጥ አግኝተናል። ስለዚህ፡ ደቂቀ እስጢፋኖሶች የሚባሉት ቢያንስ ከአነሳሳቸው ላይ እውነተኛ ቡድኖች ነበሩ ማለት ነው ወይ?” ለሚለው ጥያቄ፤
13. “ደቂቀ እስጢፋኖስ፡ ከ Knights Templars ጋር አንድነት ነበራቸው ወይ?”
14. “የኢትዮጵያ የጵጵስና መንበር፡ የአባ ሰላማ መኾን ሲገባው፡ ለምን የአቡነ ተክለሃይማኖት መንበር ኾነ? የሚቀድሙት፡ አባ ሰላማ አይደሉም ወይ? የመጀመሪያው ፓትርያርክ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን አይደሉም ወይ?”
15. “ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ፡ ለሥልጣኑ በጣም ይሳሳ ስለነበረ፡ ደቂቀ እስጢፋኖስን አሳደደ” ለሚሉ፤
16. “ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ፡ ግራ ቀኝ ሳይመረም በግንፍልተኝነት ይፈርድ የነበረ አምባገነን ነበረ” ለሚሉ፤
17. “ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ፡ ኹለት ወይም ከዚያ በላይ ሚስቶች ነበሩት” ስለሚባለው ታሪክ፤
18. “ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ፡ ስለእምነት ምንም አያውቅም፤ ፈላስፋ ነበረ” ለሚሉ፤
19. “ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ በሕይወት እያሉ ለምን አልሞገትሻቸውም ነበር?” ብለው ለሚጠይቁኝ፤
20. “ሚዛናዊ መኾን አለብን፤ ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብም፡ ብዙ ደግ ሥራዎች ቢኖራቸውም፡ ጻድቅ አይደሉም፤ ደቂቀ እስጢፋኖስም፡ አንዳንድ ትዕቢትና አፈንጋጭነት ቢኖርባቸውም፡ መናፍቃን ወይም መጥፎ ሰዎች አይደሉም። ኹለቱንም በእኩል ሚዛን ልናያቸው ያስፈልጋል” ስለሚለው አስተሳሰብ፤
21. “ከ600 ዓመታት በፊት ስለነበሩት ሰዎች ከማውራት፡ አሁን ያለውን የኢትዮጵያን ችግር ማውራት አይሻልም ወይ?” ለሚሉ፡ መልስ።
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: