ድንቅ ትምህርት በዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም 5/7/2018 ዓ.ም
Автор: ቤተ ጊዮርጊስ
Загружено: 2026-03-14
Просмотров: 67
Описание:
የጻድቁ አባታችን የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ የንግሥ በዓል በዝቋላ ደብረ ከዋክብት ገዳም በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ተከበረ
መጋቢት 5 ቀን 2018 ዓ.ም (ዝቋላ)፦
ግብፃዊውና ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (ገብረ ሕይወት) ቅዱስ ዕረፍታቸውን በማሰብ የሚከበረው ዓመታዊ የመጋቢት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በዓል፣ በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አንድነት ገዳም በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ውሏል።
በበዓሉ ላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የገዳሙ መነኮሳት፣ ካህናት፣ ዲያቆናትና ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት የመጡ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ምዕመናንና እንግዶች ተገኝተዋል።
ከምሽቱ 2 ሰዓት ጀምሮ ማኅሌተ ቅዱሳን ሲቆም ያደረ ሲሆን፣ በማለዳው ደግሞ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ያሬዳዊ ወረብና ሽብሸባ ቀርቧል። የታቦተ ሕጉን በወጣበት ወቅትም ምዕመናን በታላቅ እልልታና ዝማሬ በዓሉን አጅበው ጻድቁ ለበርካታ ዘመናት የጸለዩበት ባህር እየተዞረ ተባርኳል።
በዕለቱ በተሰጠው ትምህርተ ወንጌል ላይ፣ የጻድቁ አባታችን ገድልና ትሩፋት ለትውልድ ያለውን ፋይዳ እንዲሁም ገዳሙ ያለበትን ታሪካዊና መንፈሳዊ ጠቀሜታ በስፋት ተብራርቷል። ምዕመናንም የጻድቁን አባት በረከት ለመቀበልና የገዳሙን ቅዱስ ፀበል ለመጠመቅ ከገዳሙ ተራራ ግርጌ አንስቶ እስከ ጫፍ ድረስ በከፍተኛ ቁጥር ተገኝተዋል።
በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ የገዳሙ አስተዳደር፣ የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ከፍተኛ ጥረት ያደረጉ ሲሆን፣ የበዓሉ ተሳታፊዎችም በመንፈሳዊ እርካታና በታላቅ ደስታ በዓሉን አክብረው ወደ የቤታቸው ተመልሰዋል።
ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም፣ ጻድቁ አባት ለ562 ዓመታት በጸሎትና በብሕትውና የቆዩበት፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ ካሉ ታላላቅና ጥንታዊ ገዳማት መካከል አንዱ መሆኑ ይታወቃል።
የአባታችን ጸሎትና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን!
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: