የጥር 20 ሥንክሳር
Автор: kesisephrem
Загружено: 2026-01-27
Просмотров: 103
Описание:
ስንክሳር ዘወርኀ ጥር 20
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ሃያ በዚች ዕለት ወንጌልን ይሰብኩ ዘንድ በሽተኞችንም ይፈውሱ ዘንድ ጌታችን መርጦ ከላካቸው ከሰብዓ ሁለቱ አርድእት አንዱ የከበረ ሐዋርያ አብሮኮሮስ አረፈ ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን
በዚችም ቀን በግብጽ አገር እልፈንት ከሚባል ከተማ የከበረ ቀሲስ አክሎግ በሰማዕትነት ሞተ ። የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም ዲዮስቆርስ የናቱ ስም አፎምያ ነው እነርሱም ከከበሩ ወገኖች ውስጥ ናቸው በወርቅ በብር በላሞችና በበጎች በፈረሶችና በግመሎች እጅግ የበለጸጉ ናቸው ነገር ግን ልጅ የላቸውም ስለዚህም ያዝኑ ነበር ። ልጅንም ይሰጣቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ሲለምኑ ኖሩ ልመናቸውንም ተቀብሎ ይህን የተባረከ ልጅ ሰጣቸው ስሙንም አክሎግ ብለው ጠሩት ይህ በእግዚአብሔርዘንድ ጣዕም ያለው ይሆናል ማለት ነው ።
ስምንት ዓመትም በሆነው ጊዜ የእግዚአብሔርን ሕግ ይማር ዘንድ ለመምህር ሰጡት የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት ሁሉ ተማረ ሁል ጊዜም ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሔድ ምስጋናዎችንና ጸሎቶችን ይሰማል ይህንንም የሚያደርግ ወደ መምህርከመሔዱ አስቀድም ነው ።
በአንዲትም ዕለት ከመምህሩ ዘንድ ወጣ ወደ ቤቱም ሊሔድ በፈረስ ተቀምጦ ሁለት አገልጋዮችም ተከትለውት ሲጓዙ ብዙ ወንዶችና ሴቶች ተሰብስበው ሲጮሁ አያቸው የሆነውንም ሊያይ ወደ ርሳቸው ቀረበ ። እባብ የነከሰውና ለሞትም የቀረበ አንድ ሕፃን በመካከላቸው ወድቆ አገኘ ። የከበረ አክሎግም ይቺ ምልክት በስሜ የሚያምኑትን ትከተላቸዋለች በስሜም አጋንትን ያስወጣሉ አዳዲስ ቋንቋን ይናገራሉ የምድር አራዊቶችን በእጃቸው ይይዛሉ የሚጐዳቸውም ነገር የለም ያለውን የከበረ የወንጌልን ቃል አሰበ ።
በዚያንም ጊዜ የሕፃኑን እጅ ይዞ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ብሎ በላዩ በመስቀል ምልክት አማተበና ሕፃን ሆይ ከዚህ ክፉ እባብ መርዝ ትድን ዘንድ እናገርሃለሁ ጌታችን ንጹሕና እውነት በሆነ ቃሉ እባቡን ጊንጡን የጠላትን ኃይል ሁሉ ትረግጡ ዘንድ እነሆ ሥልጣን ሰጠኋችሁ ምንም የሚጎዳችሁ ነገር የለም ብሏልና አለ ወዲያውኑ ያ ልጅ ዳነ ከክፉ ነገርም ምንም ምን እንዳልደረሰበት ሆነ
ሕዝቡም ይህን ተአምር በአዩ ጊዜ እጅግ አደነቁ በቅዱሳኑ አድሮ ድንቅ ሥራ የሚሠራ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት የዚችም ተአምር ወሬዋ በሀገሩ ሁሉ ተሰማ ። ከመምህሩም ዘንድ ዐሥራ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ አራቱን ወንጌሎች፣ የሐዋርያትን ሥራ፣ ዐስራ አራቱን የጳውሎስን መልእክቶች፣ ሰባቱን የሐዋርያት መልእክታት፣ የዮሐንስንም ራእይ፣ መቶ ሃምሳውን የዳዊት መዝሙራት፣ የነቢያትንና የሰሎሞንን መኅልይ ጠንቅቆ አጠና ። ሁል ጊዜ በቀንና በሌሊት ያነባል በእሑድ ሌሊትም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እያገለገለ ያድራል ሁል ጊዜም አዘውትሮ ይጾማል ይጸልያል ።
ወላጆቹም ከአረፉ በኋላ ሰዎች መልካም ተጋድሎውን በአዩ ጊዜ ስለ እነርሱ ይጸልይ ዘንድ ቅስና እንዲሾምላቸው ኤጲስቆጶሱን ለመኑት እርሱ በዘመኑ ሁሉ በየሁለት ቀን በየሦስት ቀን በየሱባዔው ይጾማልና በልብሱም ውስጥ ማቅ ይለብሳልና ። ቅስና ይሾም ዘንድ የእግዚአብሔር ጸጋ ጠራችውና ኤጲስቆጶሱም ወስዶ ሳይወድ በግድ ቅስና ሾመው በተሾመ ጊዜም ለአባ አክሎግ የክህነት ሹመት ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል እያለ ሲጮህ ሕዝቡ ቃልን ሰሙ ኤጲስቆጶሱና ሕዝቡም እጅግ አደነቁ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት ።
ከእነዚያ ወራቶችም በኋላ በሀገሩ ሁሉ በክርስቲያን ወገኖች ላይ ከከሀዲዉ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ ታልቅ መከራና ስደት ሆነ አብያተ ክርስቲያናትንም አፈረሰ ብዙዎችም በሰማዕትነት ሞቱ ።
ምስክርም ይሆን ዘንድ አባ አክሎግን እግዚአብሔር ጠራው እርሱም ቆመ ወደሰማይም ቀና በማለት እንዲህ ብሎ ጸለየ ዓለሙን ሁሉ የያዝክ ጌታዬ ፈጣሪዬ መድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በሀገርህ በሁለመናዋ ላሉ ሕዝብ ቸርነትህን ይቅርታህንና ሰላምህን አድርግ ። ትባርካቸውም ዘንድ ከሰይጣናትም ስሕተት ታድናቸው ዘንድ ለእኔም ስለ ከበረው ስምህ ተጋድሎዬን እስከምፈጽም ያጸናኝ ዘንድ ቸር መልአክህን እንድትልክልኝ እለምንሃለሁ ኃይል ክብር ገንዘብህ የሆነ ለዘላለሙ አሜን ።
ከዚህም በኋላ በዙሪያው ወዳሉ ሰዎች ተመልሶ የሚሻ ይምጣ ከእኔ ጋር ይሒድ አለ የእርሱ ሰዎችና የሀገሩ ሰዎች ሦስት መቶ አርባ ተከተሉት በከፍታ ቦታ ላይም ቁመው እኛ በግልጥ ክርስቲያን ነን ብለው ጮኹ ። የንጉሡም የሠራዊት አለቃ ሰምቶ አዘነ አባ አክሎግንም አሥሮ ለመኰንኑ ለአርያኖስ ሰጠው እርሱም ለአማልክት ስገድ አለው አባ አክሎግም ለክብር ባለቤት ለጌታዬና ለፈጣሪዬ ለኢየሱስ ክርስቶስ እሰግዳለሁ እንጂ እኔ ለረከሱ አማልክት አልሰግድም አለ ።
ቢዚያንም ጊዜ መኰንኑ አርያኖስ ተቆጣ አባ አክሎግንም ጽኑ ሥቃይን አሠቃይቶ ከእሳት ማንደጃ ውስጥ ጨመረው ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ ወርዶ እሳቱን እንደ ጠል ቀዝቃዛ አደረገው አባ አክሎግም በእቶኑ መካከል ቁሞ ጸለየ ።
ከዚህም በኋላ መኰንኑ አርያኖስ ሦስት መቶ አርባውን ሰዎች እናንተ ኑ ለአማልክት ስገዱ አላቸው እነርሱም እንዲህ ብለው መለሱለት ። እኛስ ከእግዚአብሔር በቀርለረከሱ አማልክት አንሰግድም አሉት ራሶቻቸውንም በሰይፍ እንዲቆርጧቸው አዘዘና ቆረጧቸው የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ ።
በዚያንም ጊዜ የመኰንኑ የአርያኖስ ልጁ ሞተበትና እጅግ አዘነ የከበረ አባ አክሎግም በአንተ ላይ በጎ ሥራ ብሠራ ፈጣሪዬ እግዚአብሔርን ብለምነው ልጅህን ቢያስነሣልህ ምን ትሰጠኛለህ አለው አርያኖስም የመቶ አለቃ አድርጌ ሹሜ በታላቅ ክብር ወደ ሀገርህ እልክሃሁ አለው ።
የከበረ አክሎግም ይህን አልሻም ነገር ግን እንድታሠቃየኝና እንድትገድለኝ ሥጋዬንም ወደ ሀገሬ እንድትልክ ማልልኝ አለው እርሱም ማለለት ። በዚያንም ጊዜ የከበረ አክሎግ ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ብሎ ለመነ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ትሰማኝ ዘንድ ዛሬ ይህን የሞተውን ሕፃን ታስነሣው ዘንድ የከበረ ስምህም ይመሰገን ዘንድ እለምንሃለሁ ምስጋና ክብር ያንተ ነውና ለዘላለሙ አሜን
ይህንንም ሲል በመስቀል ምልክት በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በሕፃኑ ላይአማተበ ወዲያውኑ ሕፃኑ ተነሣ አሕዛብም ይህን ድንቅ ተአምር አይተው ሁሉም በአንድ ቃል በቅዱስ አክሎግ አምላክ እናምናለን ብለው ጮኹ ።
መኰንኑም ተቆጣ ከከተማም እንዲአወጧቸውና ሰፊ ጒድጓድ ቆፍረው እሳትንም አንድደው በውስጡ እንዲጨምሩዋቸው አዘዘ እንዲሁም አደረጉባቸውና ምስክርነታቸውን ፈጸሙ ቊጥራቸውም ስምንት መቶ ዘጠኝ ሆነ በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።
ከዚህም በኋላ አባ አክሎግን ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃይተው ወደ ሀገሩ ወስደው በዚያ በሰይፍ ራሱን ይቆርጡ ዘንድ አርያኖስ አዘዘ አባ አክሎግም ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ አለው እንዲህ እያለ ቁሞ ጸለየ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እኔ ባሪያህ እለምንሃለሁ ቸርነትህን በሀገሬ ላይ በውስጧም በሚኖሩ ሰዎች ሁሉ ላይ ታደርግ ዘንድ የእጃቸውንም ሥራ ባርክ ሴቶቻቸውን፣ ልጆቻቸውን፣ እንስሶቻቸውን፣ እርሻዎቻቸውንም ባርክ ከመከራም ሁሉ አድናቸው ለሥጋዬም ጸጋህን ስጠው የታመመ ሁሉ ሥጋዬ ወዳለበት መጥቶ የከበረ ስምህን ጠርቶ ወዳንተ በሚጸልይጊዜ ከደዌው ይዳን ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ሰማዕት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።
በዚችም ዕለት የሰማዕቱ የቅዱስ ብሕኑ መታሰቢያው ነው የወንጌሉ ዘወርቅ ቅዱስ ዮሐንስም ቤተክርስቲያኑ የከበረችበትና ሥጋው ወደ ሮሜ የፈለሰበት ነው ። በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን ።
በዚችም ዕለት የአባ ኖኅ፣ የአባ ስልዋኖስና፣ የአባ አብድዩ መታሰቢያቸው ነው የሰማዕት መርምህናምም ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበትና ተአምራቱ የተገለጠበት ነው ። በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን ።
ጥር ፳ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
፩.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ ሰማዕትና ጻድቅ
፪.ቅዱስ መርምሕናም ሰማዕት ቅዳሴ ቤቱ
፫.ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ ቅዳሴ ቤቱ
፬.አባ አብድዩ ጻድቅ
፭.ቅዱስ ብሕኑ ሰማዕት
፮.ቅዱስ አብሮኮሮስ ሐዋርያ የወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር
፯.አባ ኖሕ
ወርኀዊ በዓላት
፩.ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር
፪.ቅዱስ ቴዎድሮስ ሊቀ ሠራዊት
፫.ቅዱስ አሞንዮስ
፬.ቅዱስ ካሌብ ንጉሠ ኢትዮዽያ
፭.ቅድስት ሳድዥ የዋሂት
እንግዲህ ወገባችሁን በእውነት ታጥቃችሁ የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ በሰላም ወንጌልም በመዘጋጀት እግሮቻችሁ ተጫምተው ቁሙ፣ በሁሉም ላይ ጨምራችሁ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሱ ። የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ ። እርሱም የእግዚአብሔርቃል ነው ፣በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ ። በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ ። ኤፌ. ፮ ፥፲፬
@እናታችንማርያምሆይእንወድ @yekidusantarik @EfoyZeOrthodox
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: