እንደ ተቀብልኩት ምህረት መጋቢተስፋዬጋቢሶ-Revisited by-
Автор: @ADISZEMA (አዲስ ዜማ)
Загружено: 2026-01-26
Просмотров: 996
Описание:
ይህ መዝሙር የመንፈስ ቅዱስ እሳትን የሚለምን፣ ከባርነት ወደ ልጅነት የሚያመጣ የክርስቶስ ፍቅርን የሚናገር ቅዱስ መዝሙር ነው።
በደሙ ቃልኪዳን ነፃ ያደረገንን ያስታውሳል፣ እንድናገለግል ኃይል እንዲሰጠን ጌታን የሚለምን ጸሎት ነው
እንደ ፡ ተቀብልኩት ፡ ምህረት
እንደ ፡ ቸርነትህ ፡ ብዛት
እንዳገለግልህ ፡ እርዳኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ስጠኝ ፡ የመንፈስህን ፡ እሳት
እስራቴን ፡ ቆርጠህ ፡ ቀንበሬን ፡ ሰብረሃል
ነፍሴ ፡ እንድታከብርህ ፡ ነጻ ፡ አውጥተኸኛል
ባርነት ፡ አበቃ ፡ ልጅ ፡ ነህ ፡ ብለኸኛል
በደምህ ፡ ቃልኪዳን ፡ የአንተ ፡ አድርገኸኛል
እንደ ፡ ተቀብልኩት ፡ ምህረት
እንደ ፡ ቸርነትህ ፡ ብዛት
እንዳገለግልህ ፡ እርዳኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ስጠኝ ፡ የመንፈስህን ፡ እሳት
የተፍገመገመ ፡ ከውድቀት ፡ እንዲተርፍ
የደከመን ፡ ሁሉ ፡ በቃልህ ፡ እንድደግፍ
አንቃኝ ፡ በማለዳ ፡ ቀስቅሰኝ ፡ ከእንቅልፍ
ታማኝ ፡ ሎሌ ፡ አድርገኝ ፡ ልብን ፡ የሚያሳርፍ
እንደ ፡ ተቀብልኩት ፡ ምህረት
እንደ ፡ ቸርነትህ ፡ ብዛት
እንዳገለግልህ ፡ እርዳኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ስጠኝ ፡ የመንፈስህን ፡ እሳት
ስንፍናዬን ፡ አርቅ ፡ በተግሳፅህ ፡ በትር
እንድተጋ ፡ እርዳኝ ፡ ከፀጋህ ፡ ዙፋን ፡ ሥር
ኢየሱስ ፡ ያድናል ፡ ብዬ ፡ እንድመሰክር
ሕይወቴን ፡ ሙላልኝ ፡ በመስቀልህ ፡ ፍቅር
እንደ ፡ ተቀብልኩት ፡ ምህረት
እንደ ፡ ቸርነትህ ፡ ብዛት
እንዳገለግልህ ፡ እርዳኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ስጠኝ ፡ የመንፈስህን ፡ እሳት
ጥበብ ፡ ለሌላቸው ፡ ለማያስተውሉ
ለተማሩም ፡ ሰዎች ፡ አውቀናል ፡ ለሚሉ
ወንጌሉን ፡ ልናገር ፡ እንዲድኑ ፡ አምነው
ለእነዚህ ፡ ሁሉ ፡ ዕዳዬ ፡ ትልቅ ፡ ነው
እንደ ፡ ተቀብልኩት ፡ ምህረት
እንደ ፡ ቸርነትህ ፡ ብዛት
እንዳገለግልህ ፡ እርዳኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ስጠኝ ፡ የመንፈስህን ፡ እሳት
ወንጌል ፡ አይቆጠብ ፡ አይወሰን ፡ በክልል
እስከ ፡ ምድር ፡ ዳር ፡ ይሂድ ፡ ቃልህ ፡ ሳይከለከል
ለቅርቡ ፡ ለሩቁ ፡ ጽድቅህም ፡ ይታደል
የሱስን ፡ አግኝቶ ፡ ፍጥረት ፡ እሰይ ፡ ይበል
እንደ ፡ ተቀብልኩት ፡ ምህረት
እንደ ፡ ቸርነትህ ፡ ብዛት
እንዳገለግልህ ፡ እርዳኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ስጠኝ ፡ የመንፈስህን ፡ እሳት
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: