የክርስቶስ ምልጃ - መግቢያ (የእግዚአብሔር ልጅ - ክፍል 36)
Автор: Paulos Fekadu
Загружено: 2024-07-25
Просмотров: 1873
Описание:
አንዱ ሊቀ ካህናት ሲሞት ሌላው እየተተካ፣ ከአሮን ጀምሮ ሁለተኛው ቤተ መቅደስ እስከ ፈረሰበት 70 ዓ.ም ድረስ 83 ሊቃነ ካህናት እንደ ተፈራረቁ አይሁዳዊው ታሪክ ጸሓፊ ዮሴፍ ወልደ ኮርዮን ጽፏል። ሊቀ ካህናት ሁሉ በሞት ስለሚሸነፍ ክህነቱና ምልጃው በተረኛው ይወሰዳል። ያ ትውልድ ለዚህ፣ ይህ ትውልድም ለሚቀጥለው ሹመቱን ያስተላልፋል። ሁልጊዜም ግን አሸናፊው ሞት ነው። በሕይወት የሚኖር እንጂ ሟች አያማልድምና የሊቃነ ካህናቱ ምልጃ በሞት ይቋረጣል። በዚህም ላይ የኀጢአተኛ ካህን ምልጃ ዋጋ ቢስ ነው። ጌታ ኢየሱስ ግን በሕያውነቱ ቀጥሎ በዘላለማዊ ክህነት “ስለ እነርሱ እየማለደ ሁልጊዜ በሕይወት” ስለሚኖር ምልጃው አሁንም የሚካሄድ ነው።
የክርስቶስ ኢየሱስ ሊቀ ካህናዊ ምልጃ ሲነሣ፣ ተያያዥ ጥያቄዎች ብቅ ብቅ ይላሉ። በአንድ ወገን፣ የዚህን ምልጃ ምንነት በትክክል ለማወቅ የመሻት ልባዊ ጥያቄ አለ። በሌላ ወገን ደግሞ፣ ከትንሣኤው በኋላ ያለውን የክርስቶስ ሰው-ነት አሳንሶ የመመልከት ዝንባሌ ይታያል። ይህ አተያይ ግን የክርስቶስ አማላጅነት በመስቀል ላይ እንዳበቃና ከዚያ በኋላ እንደ ተዘጋ አድርጎ ወደ ማሰብ ማድረሱ አይቀሬ ነው። የክርስቶስን ሊቀ ካህንነት ከመሥዋዕትነት ሞቱ ጋር ብቻ አያይዞ ማቅረብ የሚዘወተርበት ሰበብም ከዚሁ ይመዘዛል። የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ ግን ይህ ዐይነቱን አተያይ ይቃረናል፤ “ስለ እነርሱ እየማለደ ሁልጊዜ በሕይወት ስለሚኖር” መባሉ ምልጃው አሁንም የሚካሄድ መሆኑን ያበስራልና። እንዲያውም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በመልከ ጼዴቅ ሹመት ሊቀ ካህናት ተብሎ የተጠራው ከከበረ (ከትንሣኤውና ከዕርገቱ) በኋላ ነው። አገልግሎቱም በሰማያዊቱ መቅደስ የሚካሄድ እንጂ ከመስቀሉ በፊት በምድር የነበረ አልነበረም።
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: