የልጄን ደምና እውነት እስካሁን አላገኘሁም|ከእርቁ በፊት ሀቁ ይውጣ!የደም ካሳም አንቀበልም(@gizemedia1974)
Автор: Gize Media
Загружено: 2025-12-31
Просмотров: 9180
Описание:
በኦሮሚኛ ሙዚቃዎቹ እውቅናን ያተረፈው ድምፃዊ አንዱዓለም ጎሳ፣ ከሞዴል ቀነኒ አዱኛ ህልፈት ጋር ተያይዞ ተጥሎበት ከነበረው ማህበራዊ እገዳ (Gumaata) በገዳ አባቶች ውሳኔ ነጻ መሆኑ እና ወደ ጥበብ ስራው እንዲመለስ መፈቀዱ ዛሬ ማዳውን ጀምሮ ሲሰማ የዋለ ዜና ነው፡፡ ይህ መሆኑ ደግሞ በድምፃዊው ቤተሰቦች…. ወዳጆቸ እና አድናቂዎች ዘንድ ደስታን የፈጠረ ሲሆን በቀነኒ አዱኛ ቤተሰቦች እና ከአሟሟቷ ጋር ተያየዞ አሁንም ፍትህ አልተገኘም ብለው በሚያስቡ ሰዎች ዘንድ ደግሞ ትልቅ ቅሬታን ሊፈጥር ችሏል፡፡
ትላንት ታህሳስ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በተከናወነ ሥርዓት፣ ድምፃዊው በታላላቅ አባ ገዳዎች ፊት ቀርቦ ባህላዊው የቡራኬ እና የንጻት ሥርዓት ከተፈጸመለት በኋላ፣ መደበኛ የሙዚቃ ሥራውን እንዲቀጥል ሙሉ ፈቃድ ተሰጥቶታል።
ድምፃዊው ከሞዴል ቀነኒ አዱኛ ሞት ጋር በተያያዘ በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞት የነበረ ሲሆን፣ ጉዳዩ በህግ ከመያዙ በተጨማሪ በባህላዊው መንገድ ማህበራዊ እገዳ ተጥሎበት ከሙዚቃ መድረክ ርቆ መቆየቱ ይታወሳል። ከዚህ ቀደም የተደረጉ የሽምግልና ሙከራዎች ሳይሳኩ ቢቀሩም፣ የአሁኑ የገዳ አባቶች ጣልቃ ገብነት ግን ድምፃዊው ወደ ሙያው እንዲመለስ መንገድ መክፍቱ ነው የተሰማው፡፡
በሌላ በኩል፣ የሞዴል ቀነኒ አዱኛ ቤተሰቦች ለልጃቸው ህልፈት ተጠያቂዎች ለፍርድ እንዲቀርቡና ፍትህ እንዲሰጣቸው ጥያቄያቸውን ሲያቀርቡ ቆይተዋል። አሁን አባ ገዳዎች ድምፃዊው ወደ ስራ እንዲመለስ ስለሰጡት ቡራኬ እና ውሳኔ አስመልክቶ ከቤተሰቦቹ በኩል እስካሁን የተሰጠ ይፋዊ አስተያየት የለም።
ይህ የገዳ አባቶች ውሳኔ ድምፃዊውን ከማህበራዊ እገዳው የሚያወጣው ቢሆንም፣ የሟች ቤተሰቦች የፍትህ ጥያቄ በምን ሁኔታ እንደሚቀጥል ወደፊት የሚታይ ጉዳይ ቢሆንም በሌላ መልኩ ደግሞ በአንዱዓለም ጎሳ እና በቀነኒ ቤተሰቦች መካከል የተጀመረው የዕርቅ ስነ ስርዓት ሂደት መቋረጡን የሚያመላክቱ መረጃዎች ደግሞ በስፋት እየወጡ ይገኛሉ፡፡
እንዲህ ካሉት መረጃዎች ጋር ተያየዞም የእርቅ ስርዓቱ በስምምነት እና በእርቅ ሳያልቅ እንዴት ነው ድምፃዊው ተመርቆ ስራ ይጀምር የሚባለው የሚሉ መጠይቆችም ይሰሙ ይዘዋል፡፡
ከዚህ ቀደም ከቀነኒ አዱኛ ሞት ጋር ተያየዞ ተጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ውሎ የነበረውና በኋላም በዋስ የተፈታው ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ፣ ጉዳዩ በኦሮሞ ባህላዊ የዕርቅ ሥርዓት (በአባ ገዳዎች) እንዲያልቅ ጥረት ሲያደረግ የቆይም ቢሆንም ሂደቱ ሳይሳካ መቅረቱ እና ለእርቁ ስርዓት አለመሳካት ምክንያት የሆኑ ነገሮች ሳይቀሩ ተዘርዝው ዛሬ ከሰዓት ጀምሮ ብቅ ማለት ጀምረዋል፡፡
የዕርቁ መቋረጥ ምክንያቶች፡-
የቤተሰብ ቅሬታ፡- የሟች ቀነኒ አባት አቶ አዱኛ ዋቆ፣ ድምጻዊው በዋስ መፈታቱ እንዳሳዘናቸው ገልጸው፣
"
የልጄን ደምም ሆነ እውነት እስካሁን አላገኘሁም"
ማታቸው እና ከዚህም ጋር ተያየዞ ከዚህ ቀደም በእርቅ ስርዓቱ ይደት ውስጥ
የአባ ገዳዎች ስብሰባ (ጋዲሳ)ለሦስት ጊዜያት የተካሄደ ሲሆን እዚህ ስብሰባዎችም ላይ አባት አቶ አዱና ዋቆ ተገኝተው የነበረ ቢሆህም፣ በአራተኛው ቀጠሮ ላይ ሳይገኙ መቅረታቸው ተሰምቷል።አባ ገዳ ጎበና ሆላ እንደገለጹት፣ ቤተሰቡ ለዕርቁ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው የእርቅ ሂደቱ ሊቋረጥ መቻሉን ገልፀዋል፡፡
የእውነት ፍለጋ ልዩነት፡- የሞደል ቀነኒ አባት አቶ አዱኛ ዋቆ "ገዳዮች ሳይለዩና ድርጊቱ ሳይታመን 'ጉማ' (የደም ካሳ) አንቀበልም" በሚል ሂደቱን ተችተዋል። አንዱዓለም በበኩሉ ድርጊቱን እንዳልፈጸመውና እውነቱ እንዲወጣ እንደሚፈልግ ለአባ ገዳዎቹ ሲገልጽ መቆየቱ ተገልጧል።
ከቀነኒ ሕልፍት ጋር ተያየዞ ቤተሰቦቿ አሁንም ድረስ ቀነኒ በሰው እጅ እንደተገደለች የፀና እምንት እንዳላቸው ሲናገሩ በአንፃሩ ድምፃዊ አንዱዓለም ጎሳ ግን ቀነኒ አዱና ራሷን እንዳጠፋች በመግለጽ መከራከሩ በሁለቱ ወገኖች መካከል መግባባት እንዳይፈጠር አድርጓል።
ከዚህም ጋር ተያየዞ ዛሬ ማለዳውን ጀምሮ ድምፃዊ አንዷለም ጎሳ በአባ ገዳ አባቶች ተመርቆ ወደ ቀድሞ ስራው እንዲመለስ ተፈቀደለት የሚለው መረጃ ከወጣ በኃላ ደግሞ አባት አቶ አዱኛ ዋቆ በበኩላቸው እንዲህ ሲሉ ወደ ማህበራዊ ሚዲያው ብቅ ብለው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
በመላው የኦሮሞ ዝብ መላው ኢትዮጵያ ዝብ እንድታውቁልኝ የምፈልገው ነገር ነገር ቢኖር እንደ ቀነኔ ቤተሰብ እኛ ከአባ ገዳዎች ጋር ያልተስማማንበት ቦታ ቢኖር የአባ ገዳን ስርዓት አለመቀበል አለማክበር ሳይሆን የቀነኔ ጉዳት በግልጽ ሊጣራ ይገባል ከሚል አኳያው ነው፡፡ ፊቷን እንዲያ ያደረገው …ያደረሰባት ጉዳት መጠንና ጥልቀት መታወቅ አለበት በማለት ነው፡፡
በጎጂው በኩል ማለትም በድምፃዊ አንዷለም በኩል እየተባለ ያለው አልገደልኩም ግን ጉማ እከፍላለሁ ነው እኛ ደግሞ የልጃችን ደም ሳይጣራ ጎማ እንቀበልም ….የልጃችንን ጉማ አንበላም ነው ያልነው፡፡ ከዛ ዉጪ እዛ ላይ ያልተገኘንበት ምክንያት ይሄ ነው፡፡ ሌላው ሁለቴ ቤታችን መጥተዋል የተነጋገርነው አለ ከመሃላ በፊት መጣራያት ያለበት ነገር አለ ብለን አመልክተናል አጣርቼ እመልሳለው መጨረሻ ላይ ግን አባ ገዳው ወደ መሃለ እንገባለን ነው ያሉት፡፡እኛ ደግሞ ከመኃላው በፊት ይጣራልን ነው የምንለው ብለው በቀነኒ ጉዳይ ሲያግዟቸው የነበሩትን ሁሉ አመስግነዋል፡፡
ከዚህ ቀደምም እንዲሁ በዚሁ የማህበራዊ ሚዲያው መንደር ጉዳዩን በእርቅ ሊፈቱት ነው ተብሎ ከመነገሩ ጋር ተያየዞ አባት አቶ አዱኛ ዋቆ እኛ ምንም አይነት ነገር በእርቅ የጨረስነው ነገር የለንም ጉዳዩን አሁንም ሕግ ይዞታል …ውሳኔ ያላገነ ነገር ነው ፡፡ ይህንን ነገር በማህበራዊ ሚዲያ የሚያሰራጩ ሰዎች የአንድ ወገን ብቻ መረጃ አግኝተው የሚያራግቡ ሰዎች ናቸው ከእኛ ወገን ምንም የተገጠረ አዲስ ነገር የለም ሲሉ መናገራቸው ይታወቃል
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: