ETHIOPIA - አሰብ የኢትዮጵያ የባሕር መስኮት ነው ስንል…
Автор: DireTube
Загружено: 2018-02-02
Просмотров: 34961
Описание:
ኤርትራዊያንና ኢሕአዴጋዊያን ይቺን ጉዳይ አይወዷትም፡፡አሰብ የተባለ ወደብ የኢትዮጵያ መሆኑን ማንሳት በኢሕአዴግ መንደር በጦርነት ናፋቂነት ያስከስሳል፡፡ሻዕቢያም ሆነ ኤርትራዊያን ደግሞ ኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላታችን ነች ለሚለው ትረካቸው አስረጂ አድርገው ያነሱታል፡፡
የሆነው ሆኖ አሁን አሁን አንድም የውስጥ ጉዳያችን ወጥሮ ስለያዘን፣ወዲህ ደግሞ ሰላማዊ የተቃውሞ ፖለቲካ ላይ ያሉ ኃይሎች መዳከማቸው ጉዳዩን (አጀንዳውን) የተረሳ አድርጎታል፡፡በመሆኑም በማኅበራዊ ድረ-ገጽ ውይይት ሊከፍት ይችላል በሚል ይህቺን ጽሁፍ ለመጻፍ ተነሳስቻለሁ፡
አሰብ የኢትዮጵያ ነው የሚለውን መከራከሪያ በጭራሽ ውድቅ የሚያደርግ ሕጋዊ መሠረት እንደሌለ አይተናል፡፡ይህ ባሕር የኢትዮጵያ ወደብ ነው የሚለውን ጉዳይ አንድ ጊዜ ‹‹ግመል ያጠጡበት›› ሌላ ጊዜ፣‹‹ይህንን ያነሳ እንደወንጀለኛ ይቆጠራል›› በሚል ማስፈራሪያ ከውይይት አጀንዳ እንዲርቅ ተደርጓል፡፡ኢሕአዴግና ሻዕቢያ በ1900፣1902 እና 1908 ኢትዮጵያና ጣሊያን ባደረጉት ሥምምነት አሰብ የኤርትራ ሆኗል ይላሉ፡፡በአሁኑ ወቅት ሻዕቢያንና ኢሕአዴግን የሚያስማማ ብቸኛ ጉዳይ ይህ አገላለጽ ይመስለኛል፡፡በሚከተሉት ምክንያቶች ግን አሰብ አሁንም የኢትዮጵያ አካል መሆኑን አንረሳም፡፡
1ኛ-ከላይ የተጠቀሱት ውሎች የቅኝ ግዛት ውሎች ናቸው፡፡እነዚህ ውሎች ደግሞ በተደጋጋሚ ተጥሰዋል፡፡ራሱ ጣሊያን እነዚህን ውሎች ጥሷቸዋል፡፡እናም ውሎቹ ዋጋ አጥተዋል፡፡
2ኛ-ውሎቹን የተዋዋሉት ኢትዮጵያና ጣሊያን ናቸው፡፡እናም ኤርትራ እነዚህን ውሎች ወክላ ልትከራከር አትችልም፡፡ጭራሹንም የአዲስ አበባው ስምምነት እየተባለ በሚጠራው የ1896ቱ የኢትዮጵያና የጣሊያን ውል፣ጣሊያን ኤርትራን ለቅቃ ስትወጣ ለኢትዮጵያ እንጂ ለሌላ አሳልፋ እንዳትሰጥ ተስማምተዋል፡፡
3ኛ-ጣሊያን በወቅቱ ኃያል አገር ነበረች፡፡ከላይ የተጠቀሱትን ውሎች አስገዳጅ በሆነ ሁኔታ ኢትዮጵያን ለማስፈረም መጣሯ የማይቀር ነው፡፡ለዚህ ማሳያው ውሉ ለእኩል ጥቅም ያልቆመ መሆኑ ነው፡፡ኢትዮጵያ ሰሜናዊ ግዛቷን ከማጣት በዘለለ የተጠቀመችው የለም፡፡ጣሊያን ባንጻሩ የኢትዮጵያን ሰሜናዊ ክፍል ይዟል፡፡ኃይልን በመጠቀም በሁለት አካላት መሃል የሚደረግ ስምምነት ደግሞ በየትኛውም ዓለም አቀፍ ሕግ ተቀባይነት የለውም፡፡
4ኛ-እነዚህ የቅኝ ግዛት ውሎች ተቀባይነት ይኑራቸው ቢባል እንኳ በራሱ በጣሊያን ተጥሰዋል፡፡የ1928ቱ የጣሊያን ወረራ ለዚህ ማሳያ ነው፡፡በ1908 የተደረገውን ሥምምነትና የድንበር ወሰን ጥሶ፣ኢትዮጵያን ወርሯል፡፡ከዚያ በኋላ ደግሞ ሌላ ውል አልተደረገም፡፡ራሱ ጣሊያን በወረራ ውሉን አፍርሶታል፡፡ውል ከፈረሰ ደግሞ ተቀባይነት የለውም፡፡
5ኛ-የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ከተጠናቀቀ በኋላ አሸናፊዎቹ ከጣሊያን ጋር በፓሪስ ውል ተፈራርመው ነበር፡፡በዚያ ውል መሠረት ጣሊያን በቅኝ ግዛት የያዘቻቸውን ግዛቶች ላትጠይቅ ተስማምታለች፡፡ስለዚህ አሰብ የኢትዮጵያ እንዲሆን የሚያደርግ ሌላ ሥምምነት ነው ማለት ነው፡፡
6ኛ-የያኔው የዓለም መንግሥታት ማኅበር፣በ1950ዎቹ ኤርትራን ከኢትዮጵያ ጋር በፌደሬሽን ሲያዋኅዳት የቅኝ ግዛት ውሎች ተጥሰዋል፡፡
7ኛ-በ1952 ዓ.ም. ፌደሬሽኑ ፈርሶ ኤርትራ የኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ስትሆን በወቅቱ የነበሩት ዓለም አቀፍ ሕጎች እውቅና ሰጥተውታል፡፡ይህም የቅኝ ግዛት ውሎቹ ዋጋ እንዳጡ ሌላ ማሳያ ሆኖ ይቀርባል፡፡
8ኛ-በ1964 በግብጽ ካይሮ ጉባኤ ያደረገው የያኔው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት አሰብን የራስ ገዝ አስተዳደር አድርጎ የኢትዮጵያ አካል እንዲሆን ወስኗል፡፡
እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት አስረጂዎች ጎምዛዛ እውነቶች ናቸው፡፡ኤርትራዊያንም ሆኑ ኢሕአዴጋዊያን ሊቀበሏቸው የሚገባ ወፍራም ሀቆች!! የወደብ እጦት በውድ ዋጋ (በቀን 10 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ እየከፈልን) ወደብ እንድንከራይ አድርጎናል፡፡በተለይ እንዳሁኑ የውጭ ምንዛሬ እጦት ባጋጠመን ወቅት ወደብ እያለን ለወደብ ኪራይ ረብጣ ዶላር መክፈላችን ሊቆጠቁጠን ይገባል፡፡
ፖለቲከኞቻችንም ሆኑ ዲፕሎማቶቻችን ይህንን ሐሳብ በማጎላመስ ወደ ውይይት እንዲመጣ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡ወደብ የሸቀጥ ማጓጓዣ ባሕር ብቻ አይደለም፡፡የጸጥታና የደኅንነት ጉዳይም ነው፡፡እናም ትውልድ የሚዘክረው አጀንዳ አሰብ የኛ ነው የሚለውን መሆን አለበት፡
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: