🔴 በቀጥታ፡ የዐቢይ ጾም 3ኛ " ምኩራብ" 14ኛ ቀንምኩራብ,የዐቢይ ጾም 3ኛ ሳምንት ሥርዓተ ቅዳሴ | LIVE:👉[እስመ ቅንዓተ ቤተከ በልዓኒ” መዝ 68፡9 ]
Автор: 𝗭𝗘 𝗠𝗜𝗞𝗔𝗘𝗟 𝗢𝗥𝗧𝗛𝗢𝗗𝗢𝗫 𝗠𝗘𝗗𝗜𝗔 ዘ ሚካኤል ኦርቶዶክስ ሚዲያ
Загружено: 2026-03-01
Просмотров: 473
Описание:
ምኩራብ
የዓቢይ ጾም ሦስተኛው እሁድ (14ኛው ቀን) ምኩራብ በሚል ስያሜ ይጠራል፡፡ ቅዱስ ያሬድ መድኃኔታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምኩራብ በመግባት ያስተማረውን ትምህርት መሰረት በማድርግ ምኩራብ የሚል ስያሜ ሰጥቶታል፡፡ ምኩራብ ማለት ሰቀላ፣ መሰል አዳራሽ ማለት ነው፡፡ ጌታ በአይሁድ ምኩራብ /ቤተ ፀሎት/ ተገኝቶ በቤተ መቅደሱ አካባቢ ይፈፀም የነበረውን ተገቢ ያልሆነ የመሸጥና የመለወጥ ተግባር ከተመለከተ በኋላ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት በማለት መቃወሙ ይታሰብበታል፡፡
ምኲራብ ከክርስቶስ ልደት በፊት እግዚአብሔርን ለማመስገን የእግዚአብሔር አማኞች ለጸሎት የሚሰባሰቡበት ቤት ስም ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብዙ ጊዜ ወደ ምኲራባቸው በመግባት ሰዎችን አስተምሯል፡፡ ሰዎች የእግዚአብሔር መመስገኛ የሆነውን ምኲራብ ገበያ አድርገውት ስላገኘም “ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል ተብሎ ተጽፏል እናንተ ግን የሌባና የቀማኛ ዋሻ አደረጋችሁት” /ማቴ.21፥12-13/ በማለት ገሥጾ በዚያ የሚሸጡትንና የሚለውጡትን ሁሉ በትኗቸዋል፡፡ ይህንን ምክንያት በማድረግ ሦስተኛው የዐብይ ጾም ሳምንት ምኩራብ በሚል ሰያሜ ይጠራል፡፡ በምኲራብ ገብቶ እንዳስተማረ የሚያሳስብ ዕለት የሚነበበው የወንጌል ክፍልም ዮሐ.12 እስከ ፍጻሜው ያለው ነው፡፡
ምኲራብ ማለት የአይሁድ የጸሎት ቤት ማለት ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ዘመን የአይሁድ አምልኮ በኢየሩሳሌም በነበረው ቤተ መቅደስና እንደ ሥርዓቱ የተመሠረተ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ በዚሁ መቀጠል አልቻለም፡፡ ምክንያቱም ሃይማኖት የሚያጠፋ ቤተ መቅደስ የሚያፈርስና የሚያቃጥል አረማዊ ንጉሥ ተነሣ፡፡
አረማዊው ንጉሥ ናቡከደነጾር ቤተ መቅደሱን አፍርሶ ሕዝበ እስራኤልን ወደ ባቢሎን አፍልሶ ስለነበር ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አይሁዶች በሚገኙባቸው ሥፍራዎች ሁሉ ለጸሎትና በማኅበር ለማመስገን ቤቶችን ሊሠሩ እንደጀመሩ ይነገርላቸዋል ሕዝ.11፥16፡፡
በምኩራቦችም የብሉይ ኪዳን ማምለኪያ አምልኮታቸውን ይፈጽሙ ስለነበረና ምኲራቦቻቸውም ብዙ ስለ ነበሩ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋዌ ምስጢር ተገልጾ በተዋሕዶ ከብሮ ወደ ዓለም በመጣ ጊዜም ተከታዮቹን ሐዋርያትን እየላከ በምኲራቦቻቸው ያስተምራቸው ነበር፡፡ /ማቴ.4፥23፣ ሐዋ.6፥9፣ 13፥5፣ 14፥1፣ 17፥16-18/፡፡
በብሉይ ኪዳን ታሪክና ለአይሁዳውያን ሕግ አሥር የሚያህሉ ወንዶች በአንድ ማኅበር ቢገኙ ምኲራብ ለመሥራት ይፈቀድላቸዋል፡፡ እንዲሁም በሚያንጹት ምኲራብ ውስጥ ሕግና ነቢያት የተጻፈባቸው የብር ጥቅልሎች /Scroll/ በአንድ ሳጥን ወይም ማኅደር ውስጥ ይቀመጣሉ፡፡ /ፅላትበታቦት፣ ዳዊት በማኅደር እንደሚቀመጥ/ ማለትነው፡፡ ምኲራብ እንደ ደብተራ ኦሪት ሁሉ አምልኮተ እግዚአብሔር የሚፈጽምበት ሕንፃ ነው፡፡
የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
*********************************************************
ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር እመሥዋዕት አነ ውእቱ እግዚኣ ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት እግዚኣ ውእቱ ለሰንበት ወልደ እጓለ እመሕያው ኢትግበሩ ቤተ አቡየ ቤተ ምስያጥ ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ይሰመይ ቦአ ምኩራቦሙ ወገሠፆሙ ያርምሙ አንከሩ ምህሮቶ ሞገስ ቃሉ ወጣዕመ ነገሩ ወሣዕሣዓ አፉሁ፡፡
ትርጉም:- ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ፤ ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን እወዳለሁ፤የሰንበት ጌታዋ የምሕረት አባቷም እኔ ነኝ፤ የሰው ልጅም የሰንበት ጌታዋ ነው ፡፡ያባቴን ቤት የንግድ ቦታ አታድርጉት፤ቤቴስ የጸሎት ቤት ይባላል (እያለ የሃይማኖትን ቃል አስተማራቸው፡)፡ ወደ ምኩራባቸውም ገብቶ ዝም ይሉ ዘንድ ገሠፃቸው፤ እነርሱም ትምህርቱን፣ የቃሉን ግርማ፣ የአነጋገሩን ጣዕምና፣ የአንደበቱን ቅልጥፍና አደነቁ።
ምንባባት
**************************
መልዕክታት
ቆላ. 2÷16-ፍጻ.
ያዕ. 2÷14-ፍጻ.
ግብረ ሐዋርያት የሐዋ.10÷1-8
ምስባክ
መዝ.68÷9 እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ፤ ትዕይርቶሙ ለእለይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ፤ ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ፡፡
ትርጉም፦ የቤትህ ቅንዓት በልታኛለችና የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቆአልና ነፍሴን በጾም አስመረርኋት፡፡
ወንጌል: (ዮሐ. 2÷12-ፍጻ.)
የቴሌግራም አድራሻችንን በመጫን አዳዲስ መረጃዎች ያግኙ፣ መንፈሳዊ ዕዉቀትዎን ያሳድጉ!
Zareየዐቢይ ጾም 3ኛ " ምኩራብ" 14ኛ ቀንምኩራብ new youtube # tag amahregna ena English, Tigrenya,Afaan oromoo kanbata, be hulum ቅድስት ድብግል ማ
Conversation with Gemini
You said
Zareየዐቢይ ጾም 3ኛ " ምኩራብ" 14ኛ ቀንምኩራብ new youtube # tag amahregna ena English, Tigrenya,Afaan oromoo kanbata, be hulum ቅድስት ድብግል ማርያም ይካቲት 22
#ምኩራብ #ዐቢይጾም #የካቲት22 #ቅድስትድንግልማርያም #ተዋሕዶ #ኦርቶዶክስ #ጾም #የጾምትምህርት #መዝሙር #ስብከት
#Mikurab #GreatLent #OrthodoxTewahedo #StMary #EthiopianOrthodox #LentenSeason #Christianity #FastAndPray #SpiritualGrowth
#ምኩራብ #ዓቢይጾም #ቅድስትድንግልማርያም #ተዋህዶ #የካቲት22 #ጾም #ስብከት #መዝሙር
#Mikuraab
#SoomaGuddaa #QulqulluuMaariyaam #Tawaahidoo #Ortodoxii #BarumsaAmantaa #Lallaba
#Mikuraaba #AyanaTsomu #QulqulluMaariyaamta #OrthodoxTewahido
#Torban_Sadaffaa:- “Mikuraab” jedhama.
Bakka sirni waaqeffannaan Waaqayyoo itti raawatamu fi sabni Israa’eel walitti qabaman keessaa inni tokko “Mikuraab” ture. Qulqulluun Yaareed torbee sooma guddaa sadaffaa kan inni “Mikuraab” jechuun moggaasse Gooftaan keenya Mikuraab keessatti argamuun kabaja Mana Kiristaanaa eegsisuu isaanidha. Torbee kana keessatti sagaleen Waaqayyoo dubbifamu jecha faarsaa Daawit 68:9-10 irra jiru “እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ፤ ትዕይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ፤ ወቀጻእክዋ በጾም ለነፍስየ” (“hinaaffaan mana kee na nyaateera; namoonni na arabsanis arabsoon isaanii naratti kufeera; lubbuukoos sooman nan adabe” jechuudha).
Mana kadhannaa kan taate Mana Kiristaanaa keessatti namoonni hojii foonii, daldaalaas keessati raawwachaa waan turaniif namoota keessatti kana raawwachaa turan hunda qacceen isaan garafee erga isaan arii’een booda bineeldota sanas baaseera (Yoh.2:12).
Fakkeenyuma kanaan qaama dhala namaa isa Mana Qulqullummaa Waaqayyoo jedhame kan xurreessu Waaqni akka isa adabu torbeetti baranudha (1Qor.6:16-17)
#Torban_Sadaffaa #Mikuraab
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: