የየካቲት 23 ሥንክሳር
Автор: kesisephrem
Загружено: 2026-03-01
Просмотров: 66
Описание:
ስንክሳር ዘወርኀ የካቲት 23
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅድስ ስም የካቲት ሃያ ሦስት በዚች ቀን የክቡር ፋሲለደስ ልጅ የከበረ አውሳብዮስ በሰማዕትነት ሞተ ።
ይህም የከበረ ፋሲለደስ ለአንጾኪያ መንግሥት የሠራዊት አለቃ ነው ለመንግሥት ልጆችም አባታቸው ነው እርሱም ከፋርስ ሰዎች ጋር በጦርነት ውስጥ እያለ ዲዮቅልጥያኖስ የክብር ባለቤት ጌታችንን ክርስቶስን ክዶ ጣዖትን እንዳመለከ ሰማ ። እጅግ አዝኖ ወደ ልጁ ወደ አውሳብዮስ ልኮ ይህን ነገረው የከበሩ የቤተ መንግሥት ሰዎች ዘመዶቹን ዳግመኛ ጠራቸው እነርሱም የንጉሥ ልጅ ዮስጦስ አባዲር ገላውዴዎስና ቴዎድሮስ ከእርሳቸውም ጋርያሉትን ጠርቶ ስለ ከሀዲው ንጉሥ ነገራቸው ።
ሁሉም እጅግ አዘኑ ዳግመኛም እንዲህ አላቸው እኔ ስለ ፈጣሪዬ ስለ ክርስቶስ ስም ደሜን አፈሳለሁ ሁሉም በዚህ በጎ ምክርተስማምተው እርስ በርሳቸው ተማማሉ ። ጠላቶቻቸውንም ድል አድርገው ወደ ሀገራቸው በተመለሱ ጊዜ ንጉሡ ከሠራዊቱ ጋርወጥቶ በደስታ ተቀበሏቸው ።
ከዘህም በኋላ የቅዱስ ፊቅጦር አባት ህርማኖስ ለቅዱሳኑ ጣዖትን እንዲአቀርብላቸውና አንዲሰግዱለት ንጉሡን መከረው ንጉሡም ህርማኖስ እንደ መከረው አደረገ ። በዚያንም ጊዜ ቅዱሳንን ጠርቶ እነዲህ አላቸው እኔ እጅግ እንደምወዳችሁ እናንተ ታውቃላችሁ አሁንም ለአጵሎን ሰግዳችሁ ልቤን ደስ ታሰኙ ዘንድ ከእናንተ እሻለሁ ።
ቅዱሳንም ሰምተው እጅግ ተቆጡ አውሳብዮስም ንጉሡን ሊገድል ሰይፉን መዘዘ ንጉሡም ሸሽቶ ተሸሸገ ከንጉሥም ባለሟሎች ብዙዎችን ሠራዊቱንም ጭምር ገደለ የከበረ ፋሲለደስም ባይከለክላቸው ከንጉሥ ቤት ምንም ሰው ባልቀራቸው ነበር ።
ከዚህም በኋላ ደግሞ አውሳብዮስን ወደ ግብጽ አገር ወስደው በዚያ ይገድሉት ዘንድ ህርማኖስ ንጉሡን መከረው እርሱ በዚች ሀገርከኖረ ያገር ሰዎችን በላይህ ያስነሣብሃልና ያሰብከውን ምንም ምን መሥራት አትችልም አለው ።
ንጉሡም ቅድስ አውሳብዮስን ጽኑዕ ሥቃይን ያሠቃዩት ዘንድ ወደ ግብጽ አገር ወደ ቅፍጥ ገዥ ሉልያኖስ ዘንድ እንዲወስዱት ጻፈ ወደ መኰንን ሉልያኖስም በደረሰ ጊዜ በመንኰራኵር ሕዋሳቱን በመቁራረጥ በግርፋት አሰቃዩት ። ደግመኛም በብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት ጌታችንም መልአኩን ልኮ ከመከራው ሁሉ አዳነው አጽናንቶና አረጋግቶ ያለ ጉዳት አስነሣው ።
ነፍሱንም ተድላ ደስታ ወዳለበት ገነት ወሰዳት የጻድቃንና የሰማዕታትንም መኖሪያ አየ ለርሱና ለአባቱ ለዘመዶቹም ያዘጋጀላቸውን ቦታዎች አይቶ ነፍሱ እጅግ ደስ አላት ።
ከዚህም በኋላ ወደ እሳት ማንደጃ ውስጥ ይጨምሩት ዘንድ መኰንኑ አዘዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአከ ወርዶ እሳቱን እንደ ጠል አቀዝቅዞ ያለ ጥፋት የከበረ አውሳብዮስን አወጣው ።
መኳንንቱም እንዲህ ብለው መከሩት መኰንን ሆይ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ እዘዝ ከእርሱም ትግል ታርፋለህ እርሱም የአውሳብዮስን የከበረች ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።
በዚችም ዕለት የምሥራቃዊ ቴዎድሮስ አገልጋይ የአውስግንዮስ የምስክርነቱ መታሰቢያ ነው ። በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑርለዘላለሙ አሜን ።
አምላከ ቅዱሳን ሰማዕታት ጽናታቸውን አድሎ ከበረከታቸው ይክፈለን ።
የካቲት ፳፫ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
፩.ቅዱስ ፖሊካርፐስ ሐዋርያዊ ሰማዕት የሰርምኔስ ዻዻስ
፪.ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት አባቶቻችንን አድዋ ላይየረዳበት
፫.ቅዱስ አውሳብዮስ ሰማዕት የቅዱስ ፋሲለደስ ልጅ
፬.ቅዱስ አውስግንዮስ ሰማዕት
ወርኀዊ በዓላት
፩.ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት
፪.ቅዱስ ሰሎሞን ንጉሠ እስራኤል
፫.አባ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ
፬.አባ ሳሙኤል
፭.አባ ስምዖን
፮.አባ ገብርኤል
በሰርምኔስም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልዐክ እንዲህ ብለህ ጻፍ:- ሞቶ የነበረው: ሕያውም የሆነው: ፊተኛውና መጨረሻው እንዲህ ይላል:- 'መከራህንና ድህነትህን አውቃለሁ እስከ ሞት ድረስ የታመንህ ሁን: የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለሁ ። ራእይ ፪፥፰
@እናታችንማርያምሆይእንወድ @yekidusantarik @Donkeybego
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: