ከበደ ሚካኤል - በመንጋው ተረስተው የነበሩት ታላቅ ደራሲ ፤ የልደት ቀናቸው ነው - Kebede Michael
Автор: ነበር ሚዲያ | Neber Media
Загружено: 2025-11-03
Просмотров: 621
Описание:
#nebermedia #kebedemikael #kebedemichael #birthday #derg #mengistu_hailemariam #haileselassie #ethiopia #history #mekoya #shegermekoya #ethiopia_today
የዓለም ታሪክ ፩ኛ ክፍል , ታላላቅ ሰዎች, ጃፓን እንደምን ሰለጠነች? , የስልጣኔ አየር , ብርሃነ ሕሊና , የቅኔ ውበት , የትንቢት ቀጠሮ
በመንጋው ተረስተው የነበሩት ታላቅ ደራሲ ፤ የልደት ቀናቸው ነው
Like , Share, Subscribe for more incredible stories, captivating tales from remarkable events and extraordinary lives.
Follow @NeberMedia
እኔስ ኖሬዋለሁ ሲከፋኝ ሲደላኝ
ከእንግዲህ ተወልዶ ሰው ለሚሆን ይብላኝ.....
ሲሉ የህይወት ትዝብታቸውን በቆንጆ ግጥም ነግረውን ያለፉት ታላቁ ደራሲ #ከበደ ሚካኤል ዛሬ የልደት ቀናቸው ነው....
.........
ከበደ ሚካኤል በ1971 ዓ.ም በኢትዮጵያ ራዲዮ ይተላለፍ ከነበረው “ማንን እንጠይቅ?” የራዲዮ ፕሮግራም ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ስለ መጻሕፍት፣ ስለ ጻሕፍትና ስለ ንባብ የሚከተለውን ተናግረው ነበር፡-
“… መጻሕፍትን ለማንበብ የሚጠቅሙ ነገሮች አራት ናቸው፡፡
አንደኛ፣ የሚነበበው በአንጎል ውስጥ እንዲቀረፅ ዋና ዋናዎቹን በእጅ እየገለበጡ መጻፍ፡፡
ሁለተኛ፣ ምርጥ መጻሕፍትን ጠያይቆ ማንበብ፡፡
ሦስተኛ፣ ማለፊያ መጻሕፍትን ደጋግሞ ማንበብ፡፡
አራተኛ፣ እጅግ በጣም ጥሩ መጻሕፍ ከሆነ ዋና ዋና የሆኑትን በቃል ማጥናት፡፡ …
የመጻሕፍት ዓለም አንድ ራሱን የቻለ ዓለም ነው፡፡ ወደ እሱም የሚገቡ ጥቂቶች ናቸው፡፡
መጻሕፍትን በደንብ የሚያነቡ በዓለም ላይ አሥር ሰዎች ይገኙ እንደሆነ ትልቅ ነገር ነው፡፡ እኔ ግን አሥር ሰዎች ይገኛሉ ብዬ አላምንም፡፡
ከአገራችን ደራሲያን ከተጻፉት በጣም የምወዳቸው ፦
በክቡር ብላቴን ጌታ ኅሩይ የተጻፈውን ወዳጄ ልቤ፣
ከዘነበ ኢትዮጵያዊ የተጻፈውን መጻሕፈ ጨዋታ፣
ከነጋድራስ ገብረሕይወት መንግሥትና የሕዝብ አስተዳር እና
የአጼ ምኒልክ ታሪክ፣ ከአቶ ዮፍታሔ ንጉሤ የትያትር መጻሕፍት ናቸው፡፡ …
እኔ ከሦስት ሺህ ያላነሱ መጻሕፍትን በተለያዩ ቋንቋዎች ካነበብኩኝ በኋላ ነው ልጽፍ የቻልኩት፡፡ …" ብለው ነበር...
.........
የልደት ቀናቸውን በማስመልከት በ ነበር ሚዲያ ፤ በጥበብ ነበር መሰናዶ እንዲህ ዘክረናቸዋል ፦
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: