የአለቃ ተሰማ (አባ በገና) ሙሉ የበገና መዝሙሮች | Aleka Tesema (Aba Begena) All Begena Mezmur
Автор: ቤተ በገና - Bete Begena
Загружено: 2025-08-05
Просмотров: 1806
Описание:
አለቃ ተሠማ ወልደ ዐማኑኤል/አባ በገና (1875 -1984)
▪︎ ከአለቃ ተሰማ በገናን ከተማሩ አባቶች መካከል፥ መጋቤ ስብሐት ዓለሙ አጋ፣ አቶ ገብረ ኢየሱስ፣ አቶ አድማሱ ፍቅሬ፣ አቶ ታፈሰ ተስፋዬ፣ አቶ ደምሴ ደስታ፣ አቶ ሥዩም መንግሥቱና አቶ ተድላ ተበጀ ተጠቃሽ ናቸው፡፡
▪︎ ልጃቸው አባ ወርቅነህ ተሰማ ስመ ጥር በገና ደርዳሪ ነበሩ።
▪︎ በገናቸውን እየደረደሩ ታቦተ ጽዮንን ሲያጅቡ፥ በዓሉን ታድመው ከነበሩት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓይን ውስጥ ይገባሉ። አዲስ አበባ መጥተው እንዲያስተምሩም ትእዛዝ ላኩባቸው። ሙሉ ታሪካቸውን ከታች ያንብቡ።
---
የበገናው ሊቅ አለቃ ተሰማ በቀድሞው የወሎ ክፍለ ሀገር እርቄ በምትባል አነስተኛ መንደር ውስጥ በ፲፰፻፸፭ ዓ.ም ነው የተወለዱት። አባታቸው ወልደ አማኑኤል ዘረፉ እናታቸው ደግሞ ወ/ሮ ሰገዱ ገብሬ ይባላሉ። አለቃ በዚህች በተወለዱባት አነስተኛ ከተማ ውስጥ ሆነው ከወላጆቻቸው ሳይርቁ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት የተማሩ ሲሆን እድሜያቸው ለአካለ መጠን ሲደርስም ሚስት አግብተው ቤት ንብረት አፍርተው ኖረውባታል።
የመጀመሪያ ልጃቸውን ከወለዱ በኋላ ግን በበጌ ምድር ውስጥ ወደሚገኝ ደራገር ወደ ተባለ አካባቢ ሄደው ከዜማ መሳሪያዎች ሁሉ ቁንጮ የሆነውንና፣ ከኦሪት ዘመን ጀምሮ ስብሐተ እግዚአብሔር የሚደርስበትን፣ እርኩሳን መናፍስትን አባርሮ መረጋጋት የሚያድለውን የበገና ድርደራን ለመማር ተነሱ። አስበውም አልቀሩ ወደ በጌ ምድር ተጉዘው ከመንፈቅ ላለፈ ጊዜ ትምህርቱን አጥንተው ወደ ቀያቸው ተመለሱ። ነገር ግን ቤት ንብረት ወዳፈሩበት ቀያቸው ሲመለሱ ልቡናቸውን ፍቅረ እግዚአብሔር አሸፍቶት ስለነበር ጥቂት ጊዜ ቆይተው ፈጣሪያቸውን ብቻ በሙሉ ልብ የሚያገለግሉበትን የምንኩስና ሕይወት መርጠው በመመነን የቃል ኪዳኗ ታቦት ወዳለችበት ወደ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ማርያም ሄዱ።
በዚያም እግዚአብሔር አምላክንና እናቱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን እያመሰገኑ፤ ልክ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ያደርገው እንደነበረውም ታቦተ ጽዮንን በበገና ተግተው እያወደሱ ለሰባት ዓመታት ቆዩ። ከእነዚህ ዓመታት ቆይታ በኋላ ግን እርሳቸውን ከአክሱም ጽዮን የሚለይ አንድ አጋጣሚ ተፈጠረ። ዕለቱ የአክሱም ጽዮን ማርያም ዓመታዊ በዓለ ንግሥ የሚውልበት ኅዳር ፳፩ ቀን ነው። በዚህ ታላቅ በዓል ላይ ደግሞ ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በቦታው ተገኝተዋል። እናም በዚህች ዕለት አለቃ ተሰማ ከዚህ ቀደም እንደሚያደርጉት በገናቸውን እየደረደሩ ታቦተ ጽዮንን ሲያጅቡ በጃንሆይ ዓይን ውስጥ ይገባሉ። ጃንሆይም ታዲያ በቀለ ጢሞ የሚባል አገልጋያቸውን ልከው "ይህን በበገና የመዘመር ችሎታዎትን ወደ መሀል ሀገር አዲስ አበባ መጥተው እንዲያስተምሩ አዝዣለው በላቸው" ይሉታል።
እርሱም ሄዶ ለአለቃ የተባለውን መልእክት ቢነግራቸው "እኔ ዓለምን ትቼ የመጣሁ መነኩሴ ነኝ እንደገና ወደ ዓለም መመለስ አይሆንልኝም" ብለው ይመልሱለታል። የንጉሡ አገልጋይ በቀለም ጠንከር ያለ መልሳቸውን በሰማ ጊዜ "አባታችን የንጉሥ ትዕዛዝ እምቢ አይባልም፤ ሲሆን ፈልገው በውድ አይ ካሉም በግድ ልንወስድዎ ታዘናልና እምቢ አይበሉ አላቸው።" አለቃ ተሰማም ከበዓሉ መጠናቀቅ በኋላ የንጉሡን ትዕዛዝ በማክበር ከመልእክተኞቹ ጋር አብረው ወደ አዲስ አበባ መጡ።
በዚህም ማረፊያ ቤት ተሰጥቷቸው የእንግድነት ጊዜያቸውን ከጨረሱ በኋላ በያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤትና በቀድሞው አምኃ ደስታ በአሁኑ የእንጦጦ መሰናዶ ትምህርት ቤት የበገና ድርደራን ማስተማር ጀመሩ። ይህን ጊዜ ነበር እርሳቸው ወደ ምናኔ ሲገቡ ድረውት የመጡት ልጃቸው ወርቅነህ ተሰማ "አባባ መኖሩን አለዚያም መሞቱን አውቄ እርሜን አውጥቼ ልመለስ" ብለው ከትውልድ ሀገራቸው ድረስ ለፍለጋ አዲስ አበባ የመጡት። የአሁኑ የ ፺፬ ዓመት የእድሜ ባለፀጋ የአለቃ ልጅ አባ ወርቅነህ ተሰማ ስለዛች ከአባታቸው ጋር ስለተገናኙበት ቀን ሲያስታውሱ "አባባን ዳግም ሳገኘው ከሞት የተነሳ እንጂ ለዓመታት ተለያይተን የተገናኘን አልመስልህ ብሎኝ ነበር" ይላሉ።
እናም ቁርጤን አውቄ እመጣለሁ ብለው ከሀገራቸው የወጡት አባ ወርቅነህ እንደገና ከአባታቸው መለየት ከብዷቸው ሚስታቸውንና ልጃቸውን ወደ አዲስ አበባ አምጥተው ከጎናቸው ሳይርቁ መኖር ጀመሩ። ይህን እንደገና የመወለድ ያህል ስሜት ያለው አዲስ ኑሮ መኖር ከጀመሩ ከዓመታት በኋላ ግን ዞሮ ዞሮ ከቤት ኖሮ ኖሮ ከሞት የሚቀር የለምና የእድሜ ባለፀጋው አባታቸው አለቃ ተሰማ ወልደ አማኑኤል በ፲፱፻፹፬ ዓ.ም በ፻፱ ዓመታቸው እነ መጋቤ ስብሐት አለሙ አጋን እና ደምሴ ደስታን የመሰሉ ታላላቅ ሊቃውንትን አፍርተው አረፉ።
"መስተ-ሐምም"/ለተማርያም ዘውዱ/ ፳፻፲፫ ዓ.ም
ምንጭ፤ ቤተ እንዚራ
════◉❖◉═════
ቤተ-ክርስቲያንን፣ አባቶቻችንን፣ ታሪካችንን፣ ባህል፣
ሥርዓት እና ትውፊታችንን እንወቅ!!!
Повторяем попытку...
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео
-
Информация по загрузке: